Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Digital Library

Alamat saluran: @ethiopian_digital_library
Kategori: Pekerjaan
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 65.20K
Deskripsi dari saluran

በዚህ ቻናል
👉ትምህርታዊ መፅሐፎችን
👉ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎችን
👉የሶሻልና የናቹራል መጽሐፎችን
👉የዩኒቨርስቲ እና የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
👉የጥያቄና መልስ ወርክ ሽቶችን እና
👉ልዩ ልዩ መጽሐፎችን በነፃ ያገኛሉ!
For any comments: @ethiodlbot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 13

2024-03-25 14:49:53
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች ጥሪ አድርጓል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ Freshman ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸሁን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ከመጋቢት 26 እስከ 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፦
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሰላም ግቢ
የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ አባይ ግቢ

በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታችሁን አቋርጣችሁ ለአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የሚያበቃ ውጤት ያላችሁና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞላችሁ ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል። #BahirDarUniversity

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.6K viewsedited  11:49
Buka / Bagaimana
2024-03-23 13:14:07 የአዲሱ ስርዓተ  ትምህርት መጽሀፍ ከ KG -12
New Curriculum Student Text Books from KG -12
13.8K views10:14
Buka / Bagaimana
2024-03-23 12:36:41 ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ

ለፍቶ የተማረውን ሰው ቦታ ያጣበቡ ከስራ ማባረር ብቻ ሳይሆን ከተቀጠረበት ጊዜ ጀምሮ እስከተያዘበት ቀን ድረስ የተከፈለውን ደምወዝ ከነወለዱ እንዲመልስ መደረግ አለበት። ምክንያቱም ሃሰተኛ ማስረጃ ወንጀል ነውና። #KN

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.6K viewsedited  09:36
Buka / Bagaimana
2024-03-23 12:04:45 የ2016 ፈተና መረጃ ለ6ኛ ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች

6ኛ ክፍል (ለአዲስ አበባ)
በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
አማርኛ, እንግሊዘኛ, ሒሳብ, አካ/ሳይንስ እና ሞራል ሲሆኑ ለአፋን ኦሮሞ ተማሪዎች አፋን ኦሮሞ እና ገዳ ይጨምራል
ሁሉም ፈተና የሚዘጋጀው ከ6ኛ ክፍል ብቻ(5ኛ ክፍልን አይጨምርም)

8ኛ ክፍል (ለአዲስ አበባ)
በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
አማርኛ, እንግሊዘኛ, ሒሳብ, ሶሻል ሳይንስ, አጠ/ሳይንስ, የዜግነት ት/ት እና ለአፋን ኦሮሞ ተማሪዎች አፋን ኦሮሞ እና ገዳ ይጨምራል
ሁሉም ፈተና የሚዘጋጀው ከ8ኛ ክፍል ብቻ(7ኛ ክፍልን አይጨምርም)

12ኛ ክፍል
በ2016 ዓ.ም ለፈተና የሚሰጡ የትምህርት አይነቶችን  በሁለቱም ዘርፎች ስድስት፡ ስድስት የትምህርት አይነቶች ናቸው:: እነሱም :-

ሀ/የተፈጥሮ ሣይንስ
እንግሊዝኛ, ሒሳብ, ባዮሎጅ, ፊዚክስ, ኬሚስትሪ, ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴሰት

ለ/የማህበራዊ ሣይንስ
እንግሊዝኛ, ሒሳብ, ታሪክ, ኢኮኖሚክስ, ጅኦግራፊ, ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴሰት

የፈተና ዝግጅት:-
የኢኮኖሚክስ ፈተና ከ12ኛ ክፍል ብቻ
ሌሎች የትምህርት አይነቶች ከ9ኛ -11ኛ በአሮጌው ስርአተ ትምህርት እና 12ኛ ክፍል በአዲሱ ስርአተ ትምህርት ያጠቃልላል::
ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት በነበረው አሠራር መሠረት ይቀጥላል::

ሁሉም ፈተናዎች በሰኔ ወር ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
17.3K viewsedited  09:04
Buka / Bagaimana
2024-03-23 11:15:32 የመኪናና የባጃጅ ውስጥ ስርቆት በየከተማው ተበራክቷል::
ቢያንስ ወደ መኪናና ባጃጅ ስንገባ ታርጋ መያዝ አስፈላጊ ይመስለኛል!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.8K viewsedited  08:15
Buka / Bagaimana
2024-03-23 11:12:43 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር ይሰጣል

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡

የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል።

የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡

ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.9K views08:12
Buka / Bagaimana
2024-03-22 10:59:09 ብር የወሰዱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች Bitcoin ጨምሮ ሌሎች ውድ እቃዎችን በመግዛታቸው ብሩን ለመመለስ የተቸገሩ ተማሪዎች በርካታ ናቸው

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የገንዘብ ዝውውሩ ላይ ችግር ባጋጠመው ጊዜ በርካቶች ከገንዘብ መክፈያ ማሽኖች ላይ እንዲሁም በሞባይል ባንኪንግ አማካይነት በሂሳባቸው ካላቸው የገንዘብ መጠን በላይ ማንቀሳቀስ ችለዋል።
ባንኩ እንደሚለው በዚያ ወቅት ከአስር ሺህ በላይ ግለሰቦች ከ490 ሺህ በላይ የገንዘብ ዝውውር አድርገዋል። በዚህ ሂደትም አንዳንዶች እንደሚሉት ከሚሊዮኖች እስከ ቢሊዮን መጠን ያለው ብር ተንቀሳቅሷል።

በዚህ ሁኔታ ያላሰቡትን ገንዘብ ያዘዋወሩ ተማሪዎች ብሩን የተለያዩ ውድ ቁሶችን መግዛታቸውን እና ለሌሎች ሰዎች ማስተላለፋቸውን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ተማሪዎች ገልጸዋል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲው ተማሪ እንደሚለው ብዙ ጓደኞቹ በወሰዱት ገንዘብ የተለያዩ ውድ ነገሮችን በመግዛታቸው ገንዘቡን መልሰው ማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ላይ ስላሉ ጭንቀት ላይ ይገኛሉ ይላል።
በተለይ ላፕቶፕ እና ዘመናዊ ስልኮችን የገዙ ተማሪዎች ጥቂት አለመሆናቸውን የሚጠቅሰው ተማሪው “100ሺህ ብር የሠራ አንድ ልጅ በሁለተኛው ቀን ላፕቶፕ እና ስማርት ስልክ ገዝቷል” በመግዛቱ እጁ ላይ የሚመልሰው ገንዘብ እንደሌለ ገልጿል።

“ሌሎች ደግሞ ያልተገደበ የአንድ ዓመት የኢንተርኔት ጥቅል ገዝተዋል። የነበረባቸውን ብድር የከፈሉ አሉ። . . . ብዙዎቹ ገንዘቡን ተጠቅመውበታል።”
ቢቢሲ ያነጋገረው ሌላ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሲስተም ችግር ባጋጠመበት ሌሊት ጓደኞቹ በተደጋጋሚ እየደወሉ ገንዘብ ወጪ እንዲያደርግ ቢነግሩትም “ምንም አልሠራሁም” ይላል።

ነገር ግን የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ ለማውጣት የቻሉት ጓደኞቹ ወደ እርሱ አካውንት 50 ሺህ ብር ካዘዋወሩ በኋላ የባንክ ሂሳቡ መታገዱን ይገልጻል።
“ገንዘቡን ለላከልኝ ልጅ ልመልስ ብል እንኳን አካውንቴ ታግዷል። ፈልጌ አይደለም ገንዘቡ የተላከልኝ። ትራንስፈር ስለተደረገ አካውንቴ ተዘግቶብኛል” ይላል።

ቢቢሲ ያነጋገረው ሌላኛው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ገንዘብ መውሰዱን አምኖ የወሰደውን ለመመለስ ፍቃደኛ ቢሆንም አካውንቱ በመታገዱ ተመላሽ ማድረግ አለመቻሉን ይገልጻል።

ይህ ተማሪ በሞባይል ባንኪንግ አማራጭ ወደ 70 ሺህ ብር ወደ ሌላ ባንክ አካውንት ገንዘብ ማዘዋወሩን ነገር ግን “ከሰኞ ጀምሬ ለመመለስ ብጥርም አካውንቱ እንዳይንቀሳቀስ በመደረጉ አልቻልኩም” ይላል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ችግሩ ባጋጠመበት ጊዜ ከፍተኛ መጠን ያላቸው የገንዘብ ዝውውሮች መደረጋቸውን አመልክቶ፤ በወቅቱ ግብይት ሲፈጸምባቸው የነበሩ የባንክ ሂሳቦች ማጣራት እስኪደረግባቸው ድረስ እንዲታገዱ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ባንኩ ካጋጠመው ችግር ጋር በተያያዘ የወሰዱ ሰዎች እስከ ነገ ቅዳሜ መጋቢት 14/2016 ዓ.ም. ድረስ እንዲመልሱ በድጋሚ ጠይቋል። በቀነ ገደቡ ያልመለሱትን ግለሰቦች ስምና ፎቶ በመገናኛ ብዙኃን ይፋ በማድረግ በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግም አስጠንቅቋል።

በዚህም ምክንያት ገንዘቡን ወስደው የተጠቀሙበት እንዲሁም ወደ ታገዱ አካውንቶች ያዘዋወሩ ተማሪዎች “ድንጋጤ እና ጭንቀት” ውስጥ መሆናቸውን ይናገራሉ።

ከባንኩ የወሰደውን ገንዘብ ወደ ሌላ አካውንት አዘዋውሮ ገንዘቡን ለመመለስ ተቸገርኩ ያለ ተማሪ በቅርቡ ፈተና እንዳለበት እና “ከክስተቱ ጋር በተያያዘ የስሜት መረበሽ ውስጥ እንደሚገኝ” ገልጿል። #ቢቢሲ
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.1K viewsedited  07:59
Buka / Bagaimana
2024-03-19 12:28:28 በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናዎች ላይ የተመዘገቡ ዝቅተኛ ውጤቶች የትምህርት ማህበረሰቡን አንቅቷል

በ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናዎች ላይ የተመዘገቡ ዝቅተኛ ውጤቶች የትምህርት ስርዓቱ "የወደቀባቸውን" መሰረታዊ ችግሮች በግልጽ ከማሳየት ባለፈ የትምህርት ማህበረሰቡን ማንቃታቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡

የመግቢያ ፈተናዎቹ ውጤት ማሽቆልቆል ትምህርት ቤቶች፣ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የተማሪዎች ወላጆች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጡ ማንቃቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ በትምህርት ስርዓቱ ላይ የተወሰዱ ማሻሻያዎች አውንታዊ ለውጦችን እያመጡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የለውጦቹን ፍሬ በምልዕት ለማየት ግን ጊዜ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡
በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ላይ የተመዘገቡት ዝቅተኛ ውጤቶች ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ከመላክ ባለፈ ትምህርታቸውን በቅርበት እንዲከታተሉ በር መክፈቱን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አንስተዋል፡፡

ይህ ገንቢ ልምድ ወላጆች የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከትምህርት ቤቶች እና ከመምህራን ጋር በቅርበት እንዲሰሩ ማስቻሉን "በትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ በግልጽ መታየቱን አመላክተዋል፡፡

የመለኪያ ፈተናዎቹ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በስርዓት እንዲከታተሉ፣ መምህራን በኃላፊነት ስሜት እንዲያስተምሩ፣ ርዕሳነ መምህራን የትምሀርት ሂደቱን በአግባቡ እንዲመሩ መልካም ጅምሮችን መፍጠራቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.0K viewsedited  09:28
Buka / Bagaimana
2024-03-19 12:25:39 #Ad

For English Tips, Quizzes,Tutorials and Materials!
@ethiopian_english_academy
13.0K views09:25
Buka / Bagaimana
2024-03-18 17:40:41
#China #ቻይንኛ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.1K viewsedited  14:40
Buka / Bagaimana