Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Digital Library

Alamat saluran: @ethiopian_digital_library
Kategori: Pekerjaan
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 65.20K
Deskripsi dari saluran

በዚህ ቻናል
👉ትምህርታዊ መፅሐፎችን
👉ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎችን
👉የሶሻልና የናቹራል መጽሐፎችን
👉የዩኒቨርስቲ እና የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
👉የጥያቄና መልስ ወርክ ሽቶችን እና
👉ልዩ ልዩ መጽሐፎችን በነፃ ያገኛሉ!
For any comments: @ethiodlbot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 12

2024-04-04 10:51:42
መምህርት ትዝታ ገረመው በኢትዬጵያን ቢዝነስ ሪቪዊ (Ethiopian Business Review) የመረጃ ጥንቅር እና ምርምር ኦፊሰር (Data Researcher) ሆና ከሚያዝያ 1/2016 ዓም ጀምሮ ሥራ ለመጀመር ከድርጅቱ ጋር ተፈራርማ የቅጥር ደብዳቤዋን ተቀብላለች።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.1K viewsedited  07:51
Buka / Bagaimana
2024-04-02 17:28:30 በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የቤት ኪራይ እንደሚጨምር ተገልጿል - የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ጸደቀ

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 3ኛ የሥራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ስብሰባ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን አጸደቀ።

በዛሬው ዕለት በሦስት ድምጽ ተአቅቦ ያለተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ የጸደቀው አዋጅ ቁጥር 1320/2016 በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጂጌ ማብራሪያ ሰጥተውበታል። የመንግስት ዋና ተጠሪው በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት እና ፍላጎት የተጣጣመ እንዳልሆነ ገልጸው በዚህ ሳቢያ ምክንያታዊ እና ፍትሃዊ ያልሆነ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪዎች በአገሪቱ ይስተዋላል ብለዋል።

ተስፋዬ በልጂጌ ለምክር ቤት አባላቱ እንዳስረዱት ነባራዊ ሁኔታው እና የዜጎች እሮሮ በመኖሪያ ቤት ኪራይ ላይ የመንግስት አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት አስፈላጊ በመሆኑ ይህ አዋጅ ተዘጋጅቷል። የአዋጁ ዋና ዓላማ ግልጽና ተገማች የሆነ የመኖሪያ ቤት ኪራይ አስተዳደር መዘርጋት እንዲሁም የአከራይ እና ተከራይ መብትን ሚዛናዊ ለማድረግ እንደሆነ ተገልጿል።

ስድስት ክፍሎችና 32 አንቀጾች አሉት። በውስጡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እና ዋጋ፣ የአስፈጻሚ አካላት ስልጣን እና ሌሎች ድንጋጌዎች እንደተካተቱበት ተገልጿል።

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ክፍል 2 አንቀጽ 8 ላይ የዋጋ ጭማሪን በተመለከተ ከዚህ በፊት አከራዮች በፍላጎታቸው የሚጨምሩትን ገንዘብ ተከራዮች በግዴታ መቀበል ቢኖርባቸውም፤ አሁን በመንግስት ተቆጣጣሪ አካል ጣልቃ ገብነት በዓመት አንድ ጊዜ የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታና የኢኮኖሚ ሁኔታ ታይቶ በመቶ በሚሰላ ጭማሪ ፈቃድ ብቻ የቤት ኪራይ እንደሚጨምር ተገልጿል።

በተጨማሪም የቤት አከራዮች ቅድመ ክፍያ መጠየቅ የሚችሉት የሁለት ወር ብቻ እንዲሆን የሚደነግግ ሲሆን ተከራዮችን ለማስለቀቅም የሁለት ወራት የዝግጅት ጊዜ እንዲሰጥ ያስገድዳል። ከዚህ ባለፈም መንግስት ማግኘት ያለበትን ግብር እንዲያገኝ እንደሚያስችል የምክር አባላት ተናግረዋል።

አዋጁ በተለምዶ ለአከራዮች ሰፊ እድልና መብት የሚሰጠውን ስርዓት ለማመጣጠን ያግዛልም ተብሏል።

ነምቤኦ (NUMBEO) የተባለ በሰርቢያ አገር መቀመጫውን ያደረገ የአገራትን የኑሮ ደረጃ የሚመዝኑ መረጃዎችን የሚያጋራ ድረ ገጽ የአገራቱን ዜጎች ገቢ እና የመኖሪያ ቤት ዋጋ ጥምርታን በማነጻጸር ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያውያን ለመኖሪያ ቤት የሚያወጡት ዋጋ ከገቢያቸው ላይ 43 ነጥብ 1 በመቶ እንደሆነ ተመላክቷል። #አዲስ_ማለዳ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.0K viewsedited  14:28
Buka / Bagaimana
2024-03-30 18:19:43
መምህሯን ማገዝ ለምትፈልጉ

ሙሉ ስሟ ፦ ትዝታ ገረመው ወልደ ሰማያት
ነዋሪነቷ ፦ አዲስ አበባ
የባንክ አካውንቷ ፦1000577632409 (ንግድ ባንክ)
ስልክ፦ 0904819904

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.8K viewsedited  15:19
Buka / Bagaimana
2024-03-29 18:09:08
በ2017 ትምህርት ዘመን በ11ኛ ክፍል የሥራና ተግባር ትምህርት የሚጀመርባቸውን የሙያ ዘርፍ እና አይነቶች ዝርዝር

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር በቁጥር 12/242/322/16 በቀን መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ በ2017 ትምህርት ዘመን በ8 የሙያ ዘርፍ ውስጥ 12 የሙያ ዓይነቶችን ለማስጀመር ዝርዝር ተልኮልናል፡፡

ስለሆነም በ2017 ትምህርት ዘመን ለ11ኛ ክፍል ተማሪዎች የሥራና ተግባር ትምህርት ሙያ ትምህርት ስለሚጀምሩ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ባላቸው አቅም፣ በአካባቢያቸውን ጸጋ ልየታ በማድረግ የሙያ ዘርፍ እና ዓይነት በመምረጥ ዝግጅት እንዲያደርጉ እያሳሰብን የሙያ መስኮችና ዓይነቶቹን ከዚህ ሸኚ ደብዳቤ ጋር 2 ገጽ አባሪ በማድረግ የላክን መሆኑን አሳስባለሁ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.1K viewsedited  15:09
Buka / Bagaimana
2024-03-29 13:40:40
በዓለም ብዙ ተናጋሪዎች ያሏቸው ቋንቋዎች

በአሁኑ ጊዜ በዓለም ዙሪያ ባሉ ሰዎች የሚነገሩ 7,117 የታወቁ ቋንቋዎች አሉ!

በዓለም ብዙ ተናጋሪዎች ያሏቸው ቋንቋዎች
1. እንግሊዝኛ (1, 452 ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
2. ማንዳሪን (1, 118 ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
3. ሂንዲ (602+ ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
4. ስፓኒሽ (548+ ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
5. ፈረንሳይኛ (280 ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
6. አረብኛ (274 ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
7. ቤንጋሊ (272+ ሚሊዮን ተናጋሪዎች)
8. ሩሲያኛ (258+ ሚሊዮን ተናጋሪዎች)

Source: berlitz.com

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.7K viewsedited  10:40
Buka / Bagaimana
2024-03-28 13:27:11 የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.6K viewsedited  10:27
Buka / Bagaimana
2024-03-28 12:11:01 አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 18 መምህራኑ እንደጠፉበት አስታወቀ

ጠፉ የተባሉት መምህራን የሶስተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን በመማር ላይ የነበሩ ናቸው ተብሏል:: ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ላይ ለነበሩ መምህራን ያላግባብ ከ7 ሚሊዮን በላይ ብር እንደከፈለ እና ተመላሽ እንዳላደረገ ተገልጿል::

አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 18 መምህራኑ ደብዛቸው እንደጠፉበት አስታወቀ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የኦዲት ግኝት ሪፖርት ላይ መክሯል፡፡

የቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር  እና የዩኒቨርሲቲው አመራር አባላት በጋራ ባደረጉት ውይይት ላይ እንደተገለጸው ለሶስተኛ ድግሪ በሚል ለትምህርት የተላኩ እና የጠፉ የዩንቨርሲቲው መምህራን ጉዳይ ዋነኛው ነው፡፡

የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ እና የፌደራል ዋና ኦዲተር አመራሮች ዩኒቨርሲቲው ለሶስተኛ ድግሪ ትምህርት ብሎ ስፖንሰር ሆኖ የላካቸው መምህራን በወቅቱ ትምህርታቸውን አጠናቀው እንዳልተመለሱ፣ ዩንቨርሲቲውም ለነዚህ መምህራን የከፈለውን ከ7 ሚሊዮን በላይ ብር ገንዘብ ለምን ተመላሽ አላደረክም? በሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ 18 መምህራን ትምህርታቸውን በተቀመጠላቸው ጊዜ አጠናቀው እንዳልተመለሱ፣ የመመለሻ ጊዜያቸውም እንዳለፈ መናገራቸውን በምክር ቤቱ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ በተላለፈው ላይ የቀጥታ ስርጭት ላይ ሲናገሩ ተደምጧል፡፡

በዩንቨርሲቲው ህግ መሰረት አንድ የዶክትሬት ወይም የሶስተኛ ድግሪ ትምህርትን ለማጠናቀቅ አራት ዓመት በቂ ሲሆን በተለያዩ አስቸጋሪ ምክንያቶች ትምህርቱን ማጠናቀቅ ላልቻሉ ደግሞ ሁለት ዓመት እንዲጨመርላቸው ይፈቅዳል ሲሉም ፕሬዝዳንቱ አክለዋል፡፡

ይሁንና እነዚህ የዶክትሬት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተላኩ መምህራን መካከል ትምህርታቸውን በስድስት ዓመታት ውስጥ አጠናቀው ባለመምጣታቸው ከስራ መባረራቸው ተገልጿል፡፡
እነዚህ የቀድሞ የዩንቨርሲቲው መምህራን ከስራ በመባረራቸው ምክንያት ለትምህርት ስፖንሰር፣ ደመወዝ እና ትራንስፖርት ወጪ የወሰዱትን ገንዘብ ማስመለስ አለመቻሉን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ ከ18ቱ ውስጥ አምስቱ ከሀገር ውጪ መሆናቸውን በማረጋገጣችን ዋሶቻቸው ላይ ክስ መስርተን ውሳኔው ለእኛ ተወስኖልናል ማስመለስ እንጀምራለን ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ አክለውም 15ቱ ቀሪ የቀድሞ መምህራን ግን በሀገር ውስጥ እንዳሉ እና የትኛውም ተቋም እንዳልተቀጠሩ አረጋግጠናል ነገር ግን ከደመወዛቸው እና ስራቸው ስላገድናቸው ገንዘቡን ተመላሽ ማድረግ አልቻልንም ሲሉ ለጥያቄው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ #አልአይን

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.8K viewsedited  09:11
Buka / Bagaimana
2024-03-28 09:53:30 #ቴሌግራም
# 2_ቀን_ቀረው


የቴሌግራም አዲሱን ኖትኮይን መቼም ያልሰማ የለም። ሁሉም tab tab እያደረገ መሆኑ ያያቹ ወይንም የሰማቹህ ይመስለኛል። የቢትኮይን ዋጋ እየጨመረ እየጨመረ መሄድ ያሳሰባቸው የምስራቁ ሰዎች የቴሌግራሙ መስራች ወንድማማቾች ፓቬል ዱሮቭ ከትልቁ የዲጂታል ሳንቲም አቀናባሪ TON COIN ጋር ከዚ በፊት የገባውን ስምምነት ከወራት በፊት NOTCOIN በማለት እየተንቀሳቀሰበት ይገኛል።

በጥቂት ወራት ውስጥ ቢሊዮን የዲጂታል ሳንቲሞች የተሰበሰቡ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ሳንቲሞች ያለው ሰው ወደ ዶላር ከዛም ወደ ኢትዮጲያ ብር መየቀር ይችላል። ይህ ገንዘብ ባንዴ የሚመጣበት ሳይሆን ገንዘብ መስራት የሚያስችለውን የዲጂታል መገበባያ ሳንቲም tab tab እያደረጉ በመነካካት ብቻ የሚሰራ ነው።

ዲጂታል ነገሮች በጣም ቀላል እና ግልፅ ከመሆናቸው የተነሳ ብዙ ሰዎች ይህ ውሸት ቢመስላቸውም በዛው ልክ ቢሊዮን ሳንቲሞችን ያመረተው የቴሌግራሙ NOTCOIN ከመስራቹ ፓቬል ዱሮቭ እየመጣን ነው ፍንጭ በተጨማሪ ቴሌግራም የ Official Verification የሰማያዊ ምልክት አርማን ሰጥቶታል።

ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም ከገባቹ በውሃላ start በማለት አባል ስትሆኑ PLAY ስትሉት ደግሞ ሳንቲም መስራት ትችላላችሁ አስር ጊዜ በመነካካት ፣ እኛ በሌለን ጊዜ እየነካ የሚሰራ ሮቦት AutoBot በመግዛት ፣ ጓደኞቻችንን በመጋበዝ ብዙ የዲጂታል ሳንቲሞችን መሰብሰብ እንችላለን። በቀሪ አራት ቀን ውስጥ ሙሉበሙሉ ሳንቲሙ ለገበያ የሚለቀቅ ሲሆን አሁን በመቶ ዶላሮች እየተሸጠ ይገኛል። ቀላል ነው መነካካት ብዙዙዙዙዙ የሰበሰበ የሚሰጠውን ያገኛል። ሊንኩን በመጫን ወደ NOTCOIN የዲጂታል ሳንቲም መሰብሰቢያ መግባት ትችላላቹ PLAY!!!!

ፕሮፌሰር ሄኖክ አረጋ


https://t.me/notcoin_bot?start=r_578988_34389265

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.6K viewsedited  06:53
Buka / Bagaimana
2024-03-27 11:16:20 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰዱትን ገንዘብ አልመለሱም ያላቸውን 565 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.4K viewsedited  08:16
Buka / Bagaimana
2024-03-26 16:17:10 በኦሮሚያ ክልል መሬት ያልወሰዱ መምህራን ለመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው ታዘዘ

በኦሮሚያ ክልል የመኖሪያ ቤት የሚሰሩበት መሬት ላልወሰዱ የክልሉ መምህራን ቦታ እንዲሰጣቸው የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ትእዛዝ መስጠታቸውን የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ የትምህርት ቢሮ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ ውይይት አድርጎ 8 የውሳኔ ሀሳቦችን ያስተላለፈ ሲሆን ከ8ቱ ነጥቦች አንዱ በከተማ ቤት መስሪያ ቦታ ላልወሰዱ መምህራን በአስቸኳይ ሊሰጣቸው ይገባል የሚል እንደሆነ ተጠቅሷል።

ከዚህ ቀደም መምህራኑ የቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው መመሪያ ወጥቶ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ከቆይታ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች እገዳ ተጥሎ እንደነበርና በክልሉ ት/ት ቢሮ ጥያቄ መሰረት ዳግም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ለመምህራኑ እንዲሰጣቸው ትእዛዝ መሰጠቱ ተጠቁሟል። ጉዳዩም ተፈፃሚ እንዲሆን የኦሮሚያ መሬት ቢሮ ለተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ትዕዛዝ መስጠቱም ተገልጿል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.0K viewsedited  13:17
Buka / Bagaimana