Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Digital Library

Alamat saluran: @ethiopian_digital_library
Kategori: Pekerjaan
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 65.20K
Deskripsi dari saluran

በዚህ ቻናል
👉ትምህርታዊ መፅሐፎችን
👉ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎችን
👉የሶሻልና የናቹራል መጽሐፎችን
👉የዩኒቨርስቲ እና የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
👉የጥያቄና መልስ ወርክ ሽቶችን እና
👉ልዩ ልዩ መጽሐፎችን በነፃ ያገኛሉ!
For any comments: @ethiodlbot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 11

2024-04-16 14:31:01 የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች

1.የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡

2.በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡

3.ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡

4.ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡

5. በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡

6) ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡

7.ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

8.መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

9. ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.3K viewsedited  11:31
Buka / Bagaimana
2024-04-14 09:57:27 ተማሪውና መምህሩ

አንድ ሂሣብ የማይገባው ተማሪ ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ መምህሩ ስለመቀነስ እያስተማሩ ሳለ ተማሪው ስላልገባው መምህሩ ምሳሌ ይሰጡት ጀመር፡፡

እንዲህም አሉት “አምስት በጎች በረት ውስጥ ቢኖርህና አንዱ ሾልኮ ቢያመልጥ ስንት ይቀርሃል?”

ተማሪውም “መምህር እረ ምንም አይቀረኝ” አላቸው፡፡

መምህሩም በመበሳጨት “ይህ እንዴት አይገባህም?” ብለው ጮሁበት፡፡

ተማሪውም “ኧረ መምህር የበጎችን አመል ጠንቅቄ ነው የማውቀው አንዲቷ ካመለጠች ሌሎቹም ተከትለዋት ነው የሚጠፉት” አላቸው፡፡

በዚህም ጊዜ መምህሩ ሲስቁ ክፍሉ በሙሉ ሳቀ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.8K viewsedited  06:57
Buka / Bagaimana
2024-04-14 07:06:58
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
13.9K views04:06
Buka / Bagaimana
2024-04-13 11:26:07 በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት አካል ጉዳተኞችን ያማከለ እንዲሆን ትምህርት ሚኒስቴር የተጠየቀ ቢሆንም የተሰጠዉ ምላሽ የሰብዓዊ መብትን የሚጥስ ነው ተብሏል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት አካል ጉዳተኞችን ሙሉ በሙሉ ያካተት አለመሆኑን በመገንዘብ ለጠየቅነው ጥያቄ የተሰጠን ምላሽ  የአካል ጉዳተኛን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መሆኑ እጅግ አሳዛኝ ነዉ ሲሉ የገለፁት የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ ናቸው፡፡

ከትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን ምላሽ በመገንዘብ ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቀረበው ጥያቄ መሰረት የሚፈለገውን ያህል ርቀት ለመሄድ ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግሯል ነው ያሉት፡፡

በመሆኑም አካል ጉዳተኞችን በስርዓተ ትምህርቱ በኩል አካታች ለማድረግ እንዲያስችል ለአመራሮች በቂ ግንዛቤ ሊሰጥ ይገባል ብለዋል ሀላፊው፡፡

አሐዱም የአካል ጉዳተኞችን ሰብዓዊ መብት ከማስጠበቅ አንጻር ምን እየሰራችሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን መብት ስራ ክፍል ዳይሬክተር ሜቲያ ቱምሳን ጠይቋል፡፡

ኃላፊዋ በምላሻቸውም ከትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተሰጠው ምላሽ አጥጋቢ ነው ለማለት ያስቸግራል ነው ያሉት፡፡ #አሐዱ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.9K viewsedited  08:26
Buka / Bagaimana
2024-04-13 10:11:24 ለ6ኛ ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተፈታኞች  ተማሪዎች

6ኛ ክፍል: ሞዴል ፈተና ከሚያዚያ 15 -18/8/2016 ዓ.ም - ክልል አቀፍ   ፈተና ከሰኔ 12-14/10/2016 ዓ.ም

የ8ኛ ክፍል
: ሞዴል ሚያዚያ 15 -18/8/2016 ዓ.ም -  ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 4-5/10/2016 ዓ.ም

12ኛ ክፍል : ሞዴል ፈተና ከሚያዚያ 15 -18/8/2016 ዓ.ም - ሀገር አቀፍ ፈተና  የሚምጥበት ቀን በቅርብ ይገለጻል!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.8K viewsedited  07:11
Buka / Bagaimana
2024-04-13 07:00:15
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
13.5K views04:00
Buka / Bagaimana
2024-04-12 14:03:57 ፆታዊ ጥቃት ፈጻሚዎችን የሚመዘግብ ሥርዓት ሊጀምር መሆኑን የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ

የኢትዮጵያ መንግሥት ፆታዊ ጥቃት ፈጻሚዎችን የሚመዘግብ ሥርዓት ሊጀምር መሆኑን የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

ምዝገባው ፆታን መሠረት አድርገው የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለመከላከል እና ለመቀነስ ያለመ ነው የተባለ ሲሆን፣ በተለይ “ወሲባዊ ጥቃቶች ላይ ትኩረት” እንደሚያደርግ ተነግሯል።

በሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሴቶች መብት እና ጥበቃ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ታደሰ፣ የምዝገባ ሥርዓቱን ለመጀመር 10 ሚሊዮን ብር እንደሚፈጅ ለቢቢሲ የተናገሩ ሲሆን፣ ይህ በጀት በተለያዩ አካላት መዋጮ እንደሚሸፈንም ጠቁመዋል።
ይህ ‘ብሔራዊ የፆታዊ ጥቃት ወንጀል ምዝገባ ሥርዓት’ በሚቀጥለው ዓመት ወደ ሥራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

በኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት በፊት የተደረገ ጥናት ከጠቅላላ የአገሪቱ ሴቶች 35 በመቶዎቹ የተለያዩ ዓይነት ፆታዊ ጥቃቶች እንደሚደርሱባቸው ያሳያል።

‘ብሔራዊ የፆታዊ ጥቃት ወንጀል ምዝገባ ሥርዓት’ የተሰኘው ሥርዓቱ፣ ጥቃት ፈጻሚዎች በሕግ ከታሰሩ እና ቅጣት ከተላለፈባቸው በኋላም ለዘለዓለም ተጠያቂ የሚያደርግ እና “ከተመረጡ” ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎቶች የሚያገል መሆኑ ታውቋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.6K views11:03
Buka / Bagaimana
2024-04-08 18:18:08
1445ኛው የኢድ አልፊጥር በዓል ረቡዕ ሚያዚያ 2/2016 እንደሚሆን ተረጋግጧል!

የሸዋል ወር ጨረቃ አልታየችም ፤ በመሆኑም የዒድ አልፊጥር በዓል ረቡዕ ይከበራል።

ማክሰኞ የረመዷን የመጨረሻው 30ኛ ቀን ይሆናል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛ የዒድ አልፊጥር በዓል በሰላም አደረሳቹ!

ኢድ ሙባረክ!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.7K viewsedited  15:18
Buka / Bagaimana
2024-04-05 13:24:04
ለዲግሪ 8 ዓመት መማር  ፍትሃዊ አይደለም - የመቀለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

የመቀለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዛሬዉ እለት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው ተነግሯል። ኢፍትሃዊ ያሉትን የመማር ማስተማር ሂደትን በመቃወም ላይ የነበሩት ተማሪዎቹ በጸጥታ ሃይሎች መበተናቸውም ተነግሯል።

የተማሪዎቹ ዋና ጥያቄያቸው ላለፉት በጦርነት ምክንያት የባከኑ የትምህርት ክፍለጊዜዎች እሚሰጠው የማካካሻ ትምህርት በትምህርት ሚኒስተር መመርያ መሆን አለበትም እሚል እንደሆነ ተሰምቷል።

በፀጥታ ሀይሎች የተበተኑት ሰላማዊ ሰልፈኞች "ለዲግሪ 8 አመት መማር  ፍትሃዊ አይደለም" የሚሉ መፈክሮችን ያሰሙ ሲሆን ከራያና አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምንለይበት ምንም ምክንያት የለም ማለታቸው ተነግሯል። #ዳጉ_ጆርናል

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.6K viewsedited  10:24
Buka / Bagaimana
2024-04-05 10:42:46 ‘‘የክብር ዶክትሬት ሽልማት እንጂ ለመጠሪያነት አይውልም!!

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ  ‘‘የክብር ዶክትሬት ሽልማት እና የዶክትሬት ትምህርት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ አቅራቢነት በፕሮፌሰር ሀብታሙ ወንድሙ አወያይነት መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በዚሁ ርዕሰ ላይ የገለጻና የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር::

በዚህ የገለፃና የውይይት መድረክ ላይ  የክብር ዶክትሬት ሽልማትን በተመለከተ በፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ ባቀረቡት ሰፊ የጥናት ፅሑፍ እንደገለፁት  የክብር ዶ/ር ሽልማት እንጂ ለመጠሪያነት አይውልም::

እንዲሁም ረዳት/ፕሮፌሰር ወይም ተባባሪ/ፕሮፌሰር የሚለውም ስያሜም በጋዜጠኞች ብቻ የሚሰጥ ቅፅል እንጂ ለመጠሪያነት እይውልም በማለት ተናግረዋል:: በኢትዮጵያ የክብር ሽልማት አሰጣጡ በዩንቨርስቲዎች ላይ ያለውን ችግርም በዝርዝር አንስተው ሊያስተካክሉ የሚገባቸውን ጉዳዮችንም በዝርዝር ገልጸዋል::

በተለይ ፕሮፌሰር ማስረሻ የክብር ዶክትሬትን በተመለከተ በፁሁፋቸው ላይ እንደገለፁት ከሆነ
" በየትኛውም አለም "ክቡር ዶ/ር እገሌ" ተብሎ ሲጠራ አይታወቁም :: የክብር ዶ/ር ይህ በእኛ ሐገር ብቻ በጋዜጠኞችና ከአካዳሚያዊ ክበብ ራቅ ባሉ ሰዎች  የሚጠራ ሲሆን ለዚህ ክፍተት ደግሞ የክብር ዶ/ር የሚሸልሙ ዩንቨርሲቲዎቹ የክብር ዶ/ር ለመጠሪያነት እንደማይውል ለተሸላሚዎቹና ለህዝቡ አለመግለፃቸውን እንደችግር አንስተዋል::

አያይዘውም ለነገሩ ረ/ፕ እና ተባባሪ ፕሮፌሰር የሚል መጠሪያ የሚሰማው በእኛ ሐገር ጋዜጠኞች ብቻ ነው::አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ እነዚህን ሰዎች ረ/ፕ /ተባባሪ ፕሮፌሰር( እገሌ) ብሎደብዳቤ አይፅፍላቸውም:: ዩንቨርስቲዮቹ ለእነዚህ ሰዎች አቶ (እገሌ) ብሎ ነው ደብዳቤ የሚፅፍላቸው::

ጋዜጠኞች ይህን ስያሜ የሚሰጡት ዶክተር ላልሆነ ሰው ከፍ ማድረጊያ እየመሰላቸው የሚጠሩበት ስያሜ ነው:: ለነገሩ  ባይገርማችሁ አሁን ደግሞ እጩ ዶክተር" እየተባለ መጠራት ትጀምሯል:: በማለት ተሰብሳቢውን ፈገግ አድርገውታል በማልት የገለፁ ሲሆን አያይዘውም የክብር ዶክትሬትን በተመለከተ ብቸኛዋና በጥሩ አርአያነት የምትጠቀሰው ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ ናት:: ከባህርዳር ዩንቨርስቲ የክብር ዶክተር ሽልማትን ስትቀበል "በለመደ አፋችሁ ዶክተር ብላችሁ  እንዳትጠሩኝ" ብላ የተናገረችውን አድንቀው ተናግረዋል::

እኔም ለፕሮፌሰር ማስረሻ ፕሮግራሙ ካለቀ በኃላ አንድ ጥያቄ አነሳሁላቸው "የዩንቨርሲቲው ሰዎች እኮ ናቸው ጋዜጠኞቹን በረዳት ፕሮፌሰር / በተባባሪ ፕሮፌሰር ስም ጥሩኝ የሚሉት እነሱ እንጂ ጋዜጠኛው አይደለም" ስላቸው በትህትና ወንድሜ "እነዚህ ሰዎች በራሳቸውና ባገኙት እውቀት የማይተማመኑ ሰዎች ናቸው:: እንዲህ የሚሉ ካሉ ያሳዝናሉ" ብለውኛል::

በዚህ ፕሮግራም ላይ የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ  የኢትዮጵያ በርካታ ምሁራን ተገኝተው ነበር:: #ይትባረክ_ዋለልኝ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.0K viewsedited  07:42
Buka / Bagaimana