Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Digital Library

Alamat saluran: @ethiopian_digital_library
Kategori: Pekerjaan
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 65.20K
Deskripsi dari saluran

በዚህ ቻናል
👉ትምህርታዊ መፅሐፎችን
👉ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎችን
👉የሶሻልና የናቹራል መጽሐፎችን
👉የዩኒቨርስቲ እና የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
👉የጥያቄና መልስ ወርክ ሽቶችን እና
👉ልዩ ልዩ መጽሐፎችን በነፃ ያገኛሉ!
For any comments: @ethiodlbot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 15

2024-03-12 17:27:28 #Ad

For English Tips, Quizzes,Tutorials and Materials!
@ethiopian_english_academy
13.5K views14:27
Buka / Bagaimana
2024-03-12 13:41:17
ቲክቶክ በአሜሪካ ሊታገድ ይችላል?

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በሀገሪቱ ውስጥ የቲክቶክ ተንቀሳቃሽ ምስል ማጋራትና ማየትን  ወደ መከልከል ሊያመራ የሚያስችለውን ረቂቅ ላይ እፈርማለሁ ማለታቸው ተሰምቷል።

ባይደን ቲክ ቶክን በአሜሪካ ውስጥ የሚከለክለውን ረቂቅ  ኮንግረሱ ካፀደቀው ይፈርማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ነገር ግን የሪፐብሊካኑ ተቀናቃኛቸው ዶናልድ ትራምፕ 170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የሚጠቀሙበትን አገልግሎት መከልከል ፍትሃዊ አይደለም አስጊም ነው ብለዋል።

የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ሐሙስ ዕለት በሙሉ ድምፅ ርምጃውን ካፀደቀ በኋላ በቲክቶክ ላይ በተከፈተው የማዘጋት ዘመቻ ላይ በሚቀጥለው ሳምንት ማክሰኞ  ወይም ረቡዕ  ድምጽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ቲክቶክን በአሜሪካ ለመከልከል የተዘጋጀው ረቂቅ እንዲፀድቅ የምክር ቤቱን ሁለት ሶስተኛ ድምጽ ማግኘት እንዳለበት መገለጹን የቢቢሲ ዘገባ ያመለክታል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.6K viewsedited  10:41
Buka / Bagaimana
2024-03-12 12:37:56
13.2K views09:37
Buka / Bagaimana
2024-03-12 12:37:47
12.7K views09:37
Buka / Bagaimana
2024-03-10 18:30:42 መገጣጠም

ዐብይ ፆም ሰኞ ይጀምራል!

የረመዳን ወር መግቢያም ጨረቃ በመታየቷ ሰኞ ይጀምራል!

መልካም ፆም ይሁንላችሁ!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.9K viewsedited  15:30
Buka / Bagaimana
2024-03-10 16:15:39 ትምህርት እና ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥርዓተ ትምህርት ከባሕላዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ጋር፣ በዋናነት ከኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋር የተያያዘ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ።

እ.አ.አ በ2015 በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዓመታዊ የትምህርት ኮንፈረንስ ላይ “የኢትዮጵያ የሥርዓተ ትምህርት መሠረት፣ ታሪካዊ፣ ፍልስፍናዊ፣ ሳይኮሎጂካል እና ሶሺዮሎጂካል ዕይታዎች” በሚል ርዕስ በወቅቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪ በነበሩት አወቀ ሺሺጉ የቀረበ ጥናት እንደሚያስረዳው፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የትምህርት እሳቤ የተጀመረው በስድስተኛው ክፍለ ዘመን ነው።

ጥናቱ ከሆነ እ.አ.አ በ1908 ዘመናዊ ትምህርት ወደ ኢትዮጰያ እስከገባበት ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያን የትምህርት ሥርዓትን በስርዓቷ አቅፋ ይዛ እንደነበር ያትታል።

ዘመናዊ ትምህርትን ያስተዋወቁት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ በወቅቱ ባጋጠማት የማኅበራዊ ቀውስ ምክንያት ዘመናዊ ትምህርትን በ1908 ወደ ኢትዮጵያ ማምጣታቸውን ጥናቱ ያብራራል።

ዘመናዊ ትምህርት በኢትዮጵያ እ.አ.አ 1908 በአፄ ምኒልክ ሲጀመር፣ ዓላማውም የምዕራባውያንን ሐሳቦች እና ዘመናዊነትን የመማር ፍላጎት፣ የመንግሥት ባንክ ምሥረታ፣ የድልድይ ግንባታ፣ የሆስፒታሎች፣ የሆቴሎችና የባቡር ሀዲድ ግንባታ፣ የፖስታ አገልግሎት፣ በስልክ እና ወዘተ የመሳሰሉ ፈጠራዎች አስፈላጊነት በመሆኑ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት እንደነበር ጥናቱ ያስረዳል።

የመጀመሪያው ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የተመራው በግብፃዊ ፕሮፌሰር የነበረ ሲሆን፣ በትምህርት ቤቱ ወደ 150 የሚጠጉ ብቸኛ ወንድ ልጆች ይማሩበት ነበር። ከእነዚህም መካከል አብዛኞቹ የመኳንንት ልጆች ሲሆኑ፣ ከተማሪዎቹ መካከል ልጅ ኢያሱ እና ተፈሪ መኮንን (አፄ ኃይለሥላሴ) እንደሚገኙበት ጥናቱ ያረጋግጣል።

ዘመናዊ ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ በተስፋፋበት በዚያ ወቅት ሥርዓተ ትምህርቱ እንደ ሳይንስ፣ ሂሳብ፣ ሥዕል፣ እንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ አረብኛ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የቤት አስተዳደርን ያጠቃልል ነበር።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የትምህርት ሚኒስትር የተሾመው በልጅ ኢያሱ (1906-1909) ጊዜ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ በርካታ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መከፈታቸው ይነገራል።

በትምህርት ዘርፍ ከፍተኛ እድገት የተመዘገበውም በቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ (1923-1966) ጊዜ ነው።

እድገቱ በሁሉም የትምህርት ዘርፎች ማለትም የትምህርት መዋቅር፣ የመምህራን ሥልጠና፣ የትምህርት አስተዳደር እና ትብብር እንደነበር ጥናቱ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ትምህርት ሥርዓት መንግሥታት በተቀያየሩ ቁጥር አብሮ የሚቀያየር ስለመሆኑ፣ በትምህርት ዘርፍ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል ከሚባልለት ከአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግሥት ወዲህ እንኳን ያለውን በመንግሥታቱ መቀያየር አብሮ የሚቀያየረውን የትምህርት ሥርዓትና የትምህርት መዋቅር መመልክት በቂ ማስረጃ መሆኑን የዘርፉ ምሁራን ይገልጻሉ።

ምንጭ: አዲስ ማለዳ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.8K viewsedited  13:15
Buka / Bagaimana
2024-03-08 17:43:25 በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ስራ ለአነስተኛ ዶሮ አርቢዎች የተዘጋጀ የዶሮ መኖ አዘገጃጀትና አጠቃቀም ማኑዋል

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.5K viewsedited  14:43
Buka / Bagaimana
2024-03-08 14:12:11 ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ማርች 8

የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ታሪካዊ መነሻውን ያደረገው የሠራተኞች አንቅስቃሴን ሲሆን በአሁኑ ወቅት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዕውቅና የተሰው ዓመታዊ በዓል ለመሆን በቅቷል። የክብረ በዓሏ ጅማሮ በአውሮፓውያኑ 1908 ነው በወቅቱ 15 ሺህ የሚሆኑ ሴቶች በኒውዮርክ ከተማ ላይ የሥራ ሰዓት መሻሻል (ማጠር)፣ የተሻለ ክፍያና ሴቶች በምርጫ መሳተፍ አለባቸው በሚል የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ።

ከአንድ ዓመት በኋላም የአሜሪካ ሶሻሊስት ፓርቲ የመጀመሪያዋን ብሔራዊ የሴቶች ቀን አወጀ። ቀኗን ዓለም አቀፍ የማድረግ ሃሳቡ የመጣው ክላራ ዜትኪን በምትባል ግለሰብ አማካኝነት ነው።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ይፋዊ ሆና መከበር የጀመረችው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ክብረ በዓሏን ማክበር በጀመረባት በአውሮፓውያኑ 1975 ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ "የኋላውን ማክበር፤ የወደፊቱን ማቀድ" በሚል በተባበሩት መንግሥታት ባወጣው መሪ ቃል በ1996 ነበረ በዓለም አቀፍ ደረጃ በደመቀ ሁኔታ የተከበረችው።

ዓለም አቀፏ የሴቶች ቀን የምትዘክረው ሴቶች በማኅረበሰቡ የደረሰባቸውን ጭቆናን ተቋቁመው በፖለቲካውና በምጣኔ ሀብቱ ያገኙትን ትሩፋት ትዘክራለች። ክብረ በዓሏ መሰረቷ ፓለቲካዊ ዓመፅ ሲሆን በአሁንም ወቅት በዓለም ላይ የሰፈነውን የተዛባ የሥርዓተ-ፆታ ኃይል ሚዛንን ለማስተካከል በተለያዩ ሰልፎችና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ትዘከራለች።

ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን የሚባል አለ?

አዎ አለ! ቀኑም የሚከበረው ኖቬምበር (ኅዳር) 19 ነው።
ዕለቱ መከበር የጀመረው ከአውሮፓውያኑ 1990ዎቹ በኋላ ቢሆንም ግን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዕውቅና የለውም። በዓለም ላይ ዩናይትድ ኪንግደምን ጨምሮ በ80 አገራት ይከበራል።

ዕለቱም ወንዶች በዓለም ላይ ያመጧቸውን አዎንታዊ እሴቶች፣ ለቤተሰባቸውና ለማኅበረሰቡ እያደረጉት ያለውን አስተዋፅኦ ይዘክራል። ከዚህም በተጨማሪ አርዓያ የሚሆኑ ወንዶችን ማሳየትና በወንዶች ጤንነት ላይም ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ነው።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.5K viewsedited  11:12
Buka / Bagaimana
2024-03-07 18:44:56 ዘንድሮ የሚሰጠው ልዩ የክረምት ስልጠና ለ50 ሺህ መምህራን የተዘጋጀ ነው - ትምህርት ሚኒስቴር

በዘንድሮው ዓመት ለ50 ሺህ መምህራን “ልዩ የክረምት ስልጠና” ለመስጠት፤ “አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን” የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ። በመጪዎቹ ሐምሌ እና ነሐሴ ወራት የሚሰጠው ይህ ስልጠና የቅድመ አንደኛ፣ የአንደኛ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅም ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ይህን የገለጹት፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2016 ዓ.ም. የሁለተኛው ሩብ አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት ነው። ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዚሁ ሪፖርታቸው፤ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ለትምህርት ቤት አመራሮች እና መምህራን ስለሚሰጡ ስልጠናዎች አብራርተዋል።

“በትምህርት ቤት አመራሮች ዙሪያ የአንድ ዓመት ልዩ ስልጠና ስንሰጥ ነበር” ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ በዚህ መርሃ ግብር አማካኝነትም ለ4,580 የትምህርት ቤት አስተዳዳሪዎች ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል። ለመምህራን የሚሰጥ “መደበኛ ስልጠናን” በተመለከተ ደግሞ “ባሉበት ሁኔታ ጥሩ አስተማሪዎች እንዲሆኑ ለማድረግ” ያለመ ስልጠና በመጪዎቹ ሐምሌ እና ነሐሴ ወራት እንደሚካሄድ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ለመምህራን በዩኒቨርስቲዎች ይሰጥ የነበረው ስልጠና ባለፈው ዓመት “ተዘግቶ” እንደነበር ያስታወሱት የትምህርት ሚኒስትሩ፤ ይህ የሆነበት ምክንያት በትምህርት ጥራት ረገድ ችግር በመፈጠሩ እንደሆነ አስረድተዋል። “ሁለት ሳምንት እያስተማሩ፤ ‘ተምረዋል፣ ሰልጥነዋል’ እያሉ እየለቀቁ፤ ከጥራት አኳያ በጣም ብዙ ችግር ገጥሞን ነበር” ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ ዘንድሮ የትምህርት ካሌንደሩን በማስተካከል ሁለት ወር ለስልጠና ክፍት መደረጉን አትተዋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
15.0K viewsedited  15:44
Buka / Bagaimana
2024-03-07 15:21:39 ብቻ ምን መሰለህ ትንሽ ስራ ስትጀምር የሚተችህ መብዛቱ

አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር እንደነገረኝ ከሆነ ከ7 አመት በፊት ተጨማሪ ተጓዳኝ ስራ ልጀምር ብዬ ዲሽ መግጠም ጀመርኩ አለ።

ታዲያ በሰዓቱ የገጠመኝ ነገር ይገርማል አለኝ። ምን መሰለህ የስራ ባህላችን እጅግ መቀየር አለበት! የስራ ባልደረቦቼ ሳይቀሩ አንተ እኮ ይህን ስራ መስራት የለብህም ምን ሆነህ ነው ይሉኝ ነበር። ለአንተ ይሄ አይመጥንህም ተው አታሰድበን እስከ ማለት ደርሰውም ነበር።

አንድ ቀን ደግሞ እንዲሁ ተደውሎልኝ ስሄድ የተማሪዎቼ ቤት ኖሯል ከዚያማ ከላይ ወጥቼ እየሰራሁ ቲቹ ነው እኮ እየሰራ ያለው ደሞዙ አንሶት ነው አሁን ይህን የሚሰራ ሲሉ ሰማዋቸው።

ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰፈር የሚያውቀኝ ሰው አንተ መምህርም አይደለህ ለምንድን ነው ከአቧራ ጋር የምትታገለው አሁን የመምህር ደሞዝ አልበቃህ ብሎህ ነው ሲል የዲሽ ጥገናውን እንዳቆም አሳስቦኝ ነበር።

ብቻ ምን መሰለህ ትንሽ ስራ ስትጀምር የሚተችህ መብዛቱ አለኝ!

እና አሁን የኤሌክትሮኒክስ ጥገና ከፍቼ ጥሩ የሚባል ስራ እየሰራሁ እገኛለሁ በመምህርነቱም እየሰራሁ ነው ። 

ያው እንደምታውቀው ቅርብ ጊዜ ኑሮው እጅግ በመናሩ ብዙ መምህራን ጓደኞቼ ሲቸገሩ አያለሁ እኔ ግን ብዙ ጫና ቻል አድርጌ በመስራቴ ኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም ችያለሁ ።

ሳጠቃልልህ የስራ ባህላችን በጣም መስተካከል አለበት የሚሰራን ሰው ለማደናቀፍ  የሚደረጉ ብዙ ጥረቶች አሉ ቢቻል ብናበረታታው ካልተቻለ ደግሞ ዝም ብን ሲል GA ሃሳቡን አጠቃሏል ።

እናንተስ ምን ትላላችሁ?

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.1K viewsedited  12:21
Buka / Bagaimana