ለዲግሪ 8 ዓመት መማር ፍትሃዊ አይደለም -
የመቀለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችየመቀለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዛሬዉ እለት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው ተነግሯል። ኢፍትሃዊ ያሉትን የመማር ማስተማር ሂደትን በመቃወም ላይ የነበሩት ተማሪዎቹ በጸጥታ ሃይሎች መበተናቸውም ተነግሯል።
የተማሪዎቹ ዋና ጥያቄያቸው ላለፉት በጦርነት ምክንያት የባከኑ የትምህርት ክፍለጊዜዎች እሚሰጠው የማካካሻ ትምህርት በትምህርት ሚኒስተር መመርያ መሆን አለበትም እሚል እንደሆነ ተሰምቷል።
በፀጥታ ሀይሎች የተበተኑት ሰላማዊ ሰልፈኞች "ለዲግሪ 8 አመት መማር ፍትሃዊ አይደለም" የሚሉ መፈክሮችን ያሰሙ ሲሆን ከራያና አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምንለይበት ምንም ምክንያት የለም ማለታቸው ተነግሯል። #ዳጉ_ጆርናል
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library