Get Mystery Box with random crypto!

Addis መረጃ™

Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™ A
Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™
Alamat saluran: @addis_mereja
Kategori: Berita
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 56.80K
Deskripsi dari saluran

@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹
.
⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬
⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬

መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


Pesan-pesan terbaru 7

2024-01-04 09:18:07
በደብረብርሃን ከተማ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታን ምክኒያት በማድረግ የባጃጅ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ገደብ ተጣለ!

በዛሬዉ እለት የደብረብርሃን ከተማ መስተዳድር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታውን መሠረት በማድረግ በደብረብርሃን ከተማ ለሁለት ቀናት የባጃጅ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ገደብ ኮማንድ ፖስቱ አስቀምጧል ሲል አስታዉቋል።

በደብረብርሃን ከተማ የባጃጅ ተሽከርካሪ በቀን 24 እና 25 /04/2016 ዓ/ም ማሽከርከር እንደማይቻል ኮማንድ ፓስቱ ማስታወቁን ዳጉ ጆርናል ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል። በዚህም መሠረት የባጃጅ አሽከርካሪዎች በተጠቀሱት ቀናቶች ከማሽከርከር ወይም ከእንቅስቃሴ እንዲቆጠቡም አሳስቧል።

@Addis_Mereja
16.2K viewsedited  06:18
Buka / Bagaimana
2024-01-04 09:17:38
ኢራን በቦምቦች ፍንዳታ ከ100 በላይ ሰዉ ተገደለ!

ዩናይትድ ስቴትስ የዛሬ ሶስት ዓመት ግድም በሰዉ አልባ አዉሮፕላን (ድሮን) የገደለቻቸዉ የኢራን እዉቅ ጄኔራል የቃሲም ሱሎይማኒያ ሙት አመት በሚዘከርበት ሥፍራ የፈንዱ ቦምቦች ከ100 በላይ ሰዉ ገደለ።በርካታ አቆሰለ።የኢራን ባለስልጣናት እንዳስታወቁት ሙት ዓመቱን ለመዘከር ኬርማን ከተማ በሚገኘዉ በጄኔራል ሱሌይማኒ ቀብር አጠገብ በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ሕዝብ ተሰብስቦ ነበር።

ወደ ቀብሩ በሚያመራዉ መንገድ አጠገብ የተቀበሩ ሁለት ፈንጂዎች በ15 ደቂቃ ልዩነት በተከታታይ ፈንድተዉ 103 ሐዘንተኛ ገድለዋል፤ 211 አቁስለዋል።የኢራን ባለስልጣናት «የአሸባሪዎች ጥቃት» ላሉት ፍንዳታ እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን የለም።ኢራን ዉስጥ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት ተመሳሳይ ጥቃቶችና ፍንዳታዎች ቢደርሱም የበርካታ ሰዎች ሕይወት ያጠፋ ጥቃት ሲደርስ በቅርብ ዓመታት ዉስጥ የዛሬዉ ከባዱ ነዉ።

የኢራን ፕሬዝደንት ኢብራሒም ራሲ የፀጥታ ኃይላቸዉ አደጋዉን ያደረሱትን ወገኖች አድኖ አይቀጡ ቅጣት እንደሚቀጣቸዉ ዝተዋል።የሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ጥቃቱን አዉግዘዋል።ዩናይትድ ስቴትስ አል-ቅዱስ የተባለዉን የኢራን ልዩ ጦር አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ቃሲም ሱሌማኒንና አብራቸዉ የነበሩ የኢራቅ የጦር አዛዦችን ባግድዳ አዉሮፕላን ማረፊያ አጠገብ የገደለቻቸዉ እንደ ግሪጎሪያኑ አቆጣጠር ጥር 3፣2020 ነበር።

@Addis_Mereja
14.1K viewsedited  06:17
Buka / Bagaimana
2024-01-01 18:26:55 ሰበር ዜና!

ኢትዮጵያ በሊዝ የወደብ ባለቤት መሆኗ ተሰማ!

ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች ተባለ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊ ላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ባሂ ሁሉን አካታች የሆነውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

በዚሁ መሠረት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ሆና የቆየችው ሀገራችን ከሶማሊ ላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት በሊዝ የወደብ ባለቤት መሆን ችላለች።

በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ ወደብና የጦር ሰፈር የምትገነባ ይሆናል ተብሏል።

Via EBC
@Addis_Mereja
13.9K views15:26
Buka / Bagaimana
2023-12-29 14:39:27
የቁልቢ ገብርኤል ንግሰ በአል በሰላም ተጠናቀቀ!

በየአመቱ በደማቅ ሁኔታ የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል በአል በሰላም መጠናቀቁን በቁልቢ ገብርኤል ጥበቃ የተሠማሩ የሐረሪ ፖሊስ አባላት ጥበቃ ቡድን መሪ ኮማንደር አለም ሐይሉ አስታውቀዋል።

ከሌሎች አጋር የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመቀናጀት የተሰጣቸውን ምድብ ቦታ ለተከታታይ አራት ቀናት በንቃትና በትጋት አባላቶች የተሰጣቸውን ሀላፊነት በብቃት ተወተዋል ብለዋል።

ቡድን መሪው እንደገለፁት በተመደቡበት ቦታ ሁሉ ምእመኑ ያለምንም ስጋት በአሉን ያከብር እንደነበርና በሌብነት ተሰማርተው ኪስ ሲገቡ የነበሩ ስድስት ሌቦች እጅ ከፍንጅ ተይዘው ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆኑን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከሐረሪ ፖሊስ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል።

[ዳጉ ጆርናል/Bisrat FM]
@Addis_Mereja
16.8K viewsedited  11:39
Buka / Bagaimana
2023-12-29 10:30:43 የታየ ደንደአን ጉዳይ እያጣራ መሆኑን ኢሰመኮ ገለፀ!

የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ደ’ኤታ አቶ ታየ ደንደአ ቤተሰቦች የቀረበለትን የመብት ጥሰት አቤቱታ እያጣራ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አመልክቷል።

ከታሰሩ ሁለት ሣምንት ያለፋቸውን የአቶ ታየ ደንደአን ባለቤትና የቤተሰቦቻቸውን አቤቱታዎች እየተከታተሉ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የክልሎች የክትትልና ምርመራ ዘርፍ ኃላፊ ሰላማዊት ግርማ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

የአቶ ታየ ቤተሰብ አባላት “ከመንግሥት ቤት እንድንወጣ የተደረነው ያለአግባብ ነው” ማለታቸውንና ቤተሰቡ ይጠቀምበት የነበረው የባንክ ሒሳብ መዘጋቱ ጨምሮ የቀረቡለትን አቤቱታዎች ኮሚሽኑ እየተከታተለ መሆኑንና በተመለከተ ጭምር የሚደርስበትን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ወ/ሮ ሰላማዊት አመልክተዋል።

የባለቤታቸው የባንክ ሒሳብ በመዘጋቱ ቤተሰባቸው ለችግር መጋለጡን የአቶ ታዬ ደንደአ ባለቤት ወ/ሮ ስንታየሁ አለማየሁ ተናግረዋል። እርሣቸው እንደማይሠሩና ቤተሰባቸውን እየደገፉ ያሉት በሰው እርዳታ እንደሆነ ገልፀዋል።

“በሰላም ችግር ምክንያት ከየቦታው ተፈናቅለው እኛ ጋር ተጠልለው ያሉ የቤተሰብ አባላትም በስጋት ውስጥ ናቸው” ብለዋል ወ/ሮ ስንታየሁ።

“በቀን አንዴ እየሄድን እንጎበኘዋለን። ልጆቹን ወስጄ ላሳየው ግን አልቻልኩም። የሚፈቀድልን ሦስት ደቂቃ ብቻ ነው። የክስ መዝገብ አልተከፈተበትም። ከጠበቃ ጋርም አልተገናኘም” ብለዋል።

ተዘጉ የተባሉ የባንክ ሒሳቦችና በቤተሰቡ የቀረቡ ሌሎች አቤቱታዎችን በተመለከተ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቃል አቀባይ ምላሽ ለማግኘት የእጅ ስልካቸው ላይ ጭምር በመደወል የተደረገው ጥረት አልተሳካም ።

ከመስከረም 2014 ዓ.ም. በቁጥጥር እስከዋሉበት ታህሳስ 2016 ዓ.ም. ድረስ የሰላም ሚኒስትር ደ’ኤታ ሆነው ያገለገሉት አቶ ታየ ደንደአ የኦሮሚያ ክልል ጨፌ ወይም ምክር ቤት አባል ናቸው።

Via VoA
@Addis_Mereja
15.6K viewsedited  07:30
Buka / Bagaimana
2023-12-27 22:48:07
ኢትዮጵያ ከቦንድ ባለቤቶች እየተደራደረች ነው!

ኢትዮጵያ ለቦንድ ባለቤቶች 33 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ክፍያ ሳትፈጽም ቀርታ ዕዳ መክፈል ከተሳናቸው ሀገራት ጎራ ብትመደብም ሀገሪቱ ለገባችበት ቅርቃር መፍትሔ ለማበጀት ድርድር እየተደረገ ነው። ታኅሳስ 1 ቀን 2016 መከፈል የነበረበት ወለድ በዩሮ ቦንድ ውል መሠረት የነበረው የ14 ቀናት የእፎይታ ጊዜ አብቅቷል።

ክፍያው ሳይፈጸም ወይም የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት እና የቦንድ ባለቤቶች ከአንዳች ሥምምነት ሳይደርሱ የእፎይታ ጊዜው በማብቃቱ ኢትዮጵያ ከትላንት ማክሰኞ ጀምሮ ዕዳቸውን መክፈል ከተሳናቸው ሀገራት ጎራ ተመድባለች። ኢትዮጵያ ወለድ በቀነ-ገደቡ ሳትከፍል ከቀረች በኋላ በመንግሥት እና በቦንድ ባለቤቶች መካከል የአከፋፈል ሽግሽግ ድርድር እየተደረገ እንደሚገኝ ዩኒቨርሳል ኢንቨስትመንት በተባለ ኩባንያ በኩል የኢትዮጵያ ቦንድ ባለቤት የሆነው ካፒቱሉም አሴት ማኔጅመንት ለዶይቼ ቬለ አረጋግጧል።

መቀመጫውን በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ያደረገው ካፒቱሉም አሴት ማኔጅመንት ኩባንያ የፈንድ ማኔጀር የሆኑት ቲዎዶር ኪርሽነር የኢትዮጵያ መንግሥት እና የቦንድ ባለቤቶች የየራሳቸውን ምክረ-ሐሳብ እንዳቀረቡ ለዶይቼ ቬለ በኢ-ሜይል በሰጡት ምላሽ ገልጸዋል። “አሁን ባለው ዋጋ ያን ያህል የተራራቁ አይደሉም” ያሉት ኪርሽነር የአከፋፈል ሽግሽግ ላይ የሚደረገው ድርድር ዛምቢያ ካለፈችበት ተመሳሳይ ሒደት በጣም ፈጥኖ ሊጠናቀቅ እንደሚችል ተስፋቸውን ለዶይቼ ቬለ ገልጸዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ:-

https://p.dw.com/p/4ad8G?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

@Addis_Mereja
13.2K viewsedited  19:48
Buka / Bagaimana
2023-12-26 22:30:05
የሩሲያዉ ቢትክላስተር በኢትዮጵያ የቢትኮይን የመረጃ ማዕከል ማቋቋሙን አሳወቀ!

በኢትዮጵያ የቢትኮይን ማይኒንግ የመረጃ ማዕከል ማቋቋሙን ያሳወቀዉ ቢትክላስተር በአዲስ አበባ ከፍተኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ ጣቢያ ባለበት ቂሊንጦ አከባቢ መሆኑን ገልጿል።

የሩሲያው የቢትኮይን ማይኒንግ አቅራቢ ድርጅቱ አዲሱ የመረጃ ማዕከል ሥራዉ ከወር በኃላ እንደሚካሄድ በመግለፅ አሁን ላይ በ 30,000 ካሬ ሜትር ላይ ትራንስፎርመሮች የማገናኘት ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁሟ።

በቢትኮይን የሚፈፀሙ ግብይቶች አስተማማኝ እና እምነት የሚጣልባቸው መሆናቸዉን ለማረጋገጥ የማረዳ ስርዓት መሆኑ የተነገረለት የመረጃ ማዕከሉ 100 ፐርሰንት የኤሌክትሪክ ኃይል ከታዳሽ የኃይል ምንጮች በተለይ ከታላቁ ህዳሴ ግድብ የሚቀርብ መሆኑን አሳዉቋል። በኢትዮጵያ 120 ሜጋ ዋት የቢትኮይን የመረጃ ማዕከል ለማቋቋም የወሰነዉ ቢትክሉስተር ለሀገሪቱ ትልቅ የኢኮኖሚ ጥቅም አለዉ ሲልም ገልጿል።

Via Capital
@Addis_Mereja
13.3K viewsedited  19:30
Buka / Bagaimana
2023-12-26 22:30:04 በአራብሳ ኮንዶሚኒየም በተሽከርካሪ የታገዘ የወንጀል ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑ ተገለፀ!

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ለሚፈጠሩት የስርቆት እና የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ምክንያቱ የፖሊስ ጣቢያ በበቂ ሁኔታ ባለመኖሩ መሆኑን የአካባቢው የሰላም ሰራዊት አስታውቋል፡፡

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የአራብሳ ኮንዶሚኒየም የወረዳ አራት የሰላም ሰራዊት አስተባባሪ አቶ አደመ ደምሴ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን እንደተናገሩት በአካባቢው የሚፈፀሙ ወንጀሎች እየተበራከቱ እንደሆኑ በመግለፅ በተሽከርከሪ የታገዘ የወንጀል ድርጊት እንደሚፈፀም ተናግረዋል

ወንጀሉን ፈፃሚዎቹ ቪትስ እና መሰል ተሽከርካሪዎችን እየተከራዩ ከሶስት ሰው በላይ በመሆን በነዋሪው መግቢያና መውጫ ሰዓት ላይ በስለት በማስፈራራት የሴቶችን ቦርሳ እና የወንዶችንም ስልክ እና ብር ይዘርፋሉ፡፡ እንዲሁም ወንጀለኞቹ ከሌላ አካባቢ እንደሚመጡ እና ከመኪና በተጨማሪ በባጃጅ ነዋሪውን አሳፍረው ወደ ሌላ ቦታ በመውሰድ ስርቆት እንደሚፈፅሙ ገልፀዋል፡፡

ለዚህ ወንጀል መበራከት ደግሞ ዋነኛ ምክንያቱ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ለሁለት ወረዳ አገልግሎት ስለሚሰጥ እና የፖሊስ አባል እጥረት በመኖሩ እና በቂ የመንገድ ብሎም የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት አለመሟላት አስተዋጽኦ አድርጓል።

የመንገድ መብራት እንዲሰራ ብንጠይቅም መፍትሄ ግን እስካሁን አልተሰጠውም ብለዋል፡፡ወንጀሉም ጨለማን ተገን በማድረግ እየተሰራ እንደሆነ እና በአካባቢው ያለው የሰላም ሰራዊትም ሁሉም የቤተሰብ ሀላፊ ስለሆነ እስከተወሰነ ሰዓት ድረስ ብቻ እንደሚጠብቅ አክለዋል። እስካሁን በሰው ህይወት ላይ የደረሰ አደጋ ባይኖርም ለነዋሪው ግን በሰላም ወጥቶ መግባቱ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን አቶ አደመ ደምሴ ጨምረው ተናግረዋል፡፡

Via Bisrat FM
@Addis_Mereja
13.5K viewsedited  19:30
Buka / Bagaimana
2023-12-23 23:48:31
Russia and Ethiopia are becoming close friends!

Judge for yourself: Ethiopia has finally joined BRICS. Both countries oppose neocolonialism and support getting rid of the dollar in international trade. As you know, there are many Orthodox and Muslims in both countries.

If you want to find out more news about BRICS, de-dollarisation, Russia-Ukraine conflict and the uprising multipolar world, join Geopolitics Live channel.

Huge thanks to all our pals who are already with us, and welcome to our new readers! @geopolitics_live

@Addis_Mereja
15.6K viewsedited  20:48
Buka / Bagaimana
2023-12-22 22:42:24
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይቅርታ ጠየቀ!

በዛሬው ቀን ለመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኞች ሊሰጥ ታቅዶ የነበረው ፈተና መስጠት ባለመቻሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይቅርታ ጠይቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለመረጠው ህዝብ በታማኝነት እና በብቃት ለማገልገል ካለው ጽኑ ፍላጎት በመነሳት በመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተገልጋዩን ህብረተሰብ እንግልት ለመቀነስ የሪፎርም ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለአመራሮች፣ ለባለሙያዎች እና ለሰራተኞች ፈተና እንዲሰጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነት መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ሆኖም ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና በቴክኒክ ችግር ምክንያት በመሰረዙ ዩኒቨርስቲው ይቅርታ ጠይቋል፡፡  ነገር ግን የተዘጋጀው ፈተና የደህንነት ችግር ያላጋጠመው መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን ብሏል በላከው ደብዳቤ፡፡ ቀጣይ ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ በቅርብ ይፋ እንደሚደረግም ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

@Addis_Mereja
16.9K viewsedited  19:42
Buka / Bagaimana