Get Mystery Box with random crypto!

Addis መረጃ™

Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™ A
Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™
Alamat saluran: @addis_mereja
Kategori: Berita
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 56.80K
Deskripsi dari saluran

@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹
.
⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬
⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬

መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


Pesan-pesan terbaru 5

2024-02-06 12:41:57 በፀጥታ ጉዳይ ጠቅላይ ሚንስተሩ ለፓርላማው ከሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች

የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ አንኳር ጉዳዮች የፖለቲካ ፍላጎትን ለማሳካት የሚኬድባቸው መንገዶች ችግር ያለባቸው መሆኑ ነው፤

ማንኛውም ችግር ሲያጋጥም ያንን ችግር ለመፍታት በንግግር ለመፍታት ያለን ልምምድ እየቀነሰ መምጣትም ሌላው ችግር  ነው፤

ለሰላም ለሚደረግን ጉዞ ወጥመድ የሚቀመጥበት ልምምዱም የሰፋ መሆኑ ሌላ ችግር ነው፤

እነዚህ ችግሮች አብዛኛው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማዕከል አድርጎ የሚነሳ አይደለም፤ ቢሆን ኖሮ ለቀይ ባህር  እድል ለመፍጠር የምናደርገውን ጥረት ባልተቃወሙት ነበር፤

ታንዛኒያ ከሸኔ ጋር የነበረውን ድርድር ስንጀምር ለመላው ህዝብ ነግረን አሳውቀን ሳንደብቅ ነው፤ ውጤቱ ግን ምንም የሚጨበጥ ስላልሆነ ምንም ማለት አልቻልንም፤

ሸኔ በአስመራ በነበረው ድርድር ቃል የተገባው ሳይፈጸም ቀርቶ ከሆነ ጫካ የገባው፤ እታገላለሁ የሚልለትን ህዝብ ማገትና ማሰቃየት ላይ ነው፤ የራስን ህዝብ እያሰቃዩ እታገልልሃለሁ ማለት ዋጋ የለውም፤

  ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ በጠበንጃ ስልጣን መያዝ አይቻልም፤ የሚቻለው በሰላም በንግግር ነው፤

በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች ከከሚሴ በስተቀር ከህዝብ ጋር ለመነጋገር እድል አግኝቻለሁ፤ ጥያቄያቸው የልማት፣ የወሰን ይገባኛል እና የህገ መንግስት ነው፤

በአማራ ክልል ባለፉት አምስት አመታት 3 ሺህ 200 ኪሎሜትር መንግድ ጀምረነ እየሰራን ነው፤

ይህ መንገድ በክልሉ ውስጥ  ዞንን ከዞን ወረዳን ከወረዳ  ጋር የሚያገናኝ ነው፤

ይህ መንገድ አንድ ሽሮ ፈሰስ የሚባል አይደለምዐ ከትውልድ ትውልድ የሚተላለፍ ነው፤

ከአማራ ክልል የተነሳውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ መንግስት የሄደበትን ርቀት አመላካች ነው፤ በቂ አይደለም፤

ከመንገድ ባሻገር በቱሪዝም መስክም የጎርጎራ ፕሮጀክት በአይነትና በደረጃው የትም ያልተሰራ ፕሮጀክት ሆኖ እየተሰራ ነው፤

የላሊበላን ቅርስም ለማደስ የፈረንሳይን ፕሬዝዳንት ሳይቀር ይዘን ሄደነ አሳይተነ እያሰራን ነው፤ በሰላም ምክንያት ወጣ ገባ ቢልም፤

ፋሲልንም የፈረሰውን ማስጎብኘት ተገቢ አይደለም ብለን፤ ስራውን ለማስጀመር ሙከራ አድረገነ ነበር፤ ነገር ግን በተለያዩ አሉባልታዎች ስራውን አስቁመውታል" ብለዋል።

@Addis_Mereja
13.7K viewsedited  09:41
Buka / Bagaimana
2024-02-01 09:36:57
በአውሮጳ የሴቶች ግርዛት እየተስፋፋ ነው!

አስከፊው የሴቶች ግርዛት በአውሮጳም እየተስፋፋ ነው ሲል ቴር ደ ፋም የተባለው የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅት አሳሰበ።በድርጅቱ ግምት በአሁኑ ጊዜ ጀርመን ውስጥ ብቻ የተገረዙ ከ100 ሺህ በላይ ልጃገረዶች ይገኛሉ።ሌሎች ከ17 ሺህ በላይ እንደሆኑ የሚገመቱ ልጃገረዶች ደግሞ ለግርዛት የተጋለጡ ናቸው ብሏል ድርጅቱ።

በፕላን ኢንተርናሽናል የህጻናት መብቶች አዋቂ ኤዴል ኦትየኖ ዖኮት ከዚህ በመነሳት ከአጋር ድርጅቶች ጋር ስለ ሴቶች ግርዛት አደገኛነት ግንዛቤ ለማስጨበጥ እንደሚፈልጉ መግለጻቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት ድርጅት DPA ዘግቧል።በመላ ጀርመን የግርዛት ሰለባ ለሆኑ ቤተሰቦች ድጋፍ የሚያደርጉ በርካታ የምክር አገልግሎት መስጫዎች ቢኖሩም ለህክምና ባለሞያዎች ለአዋላጆች፣ለህጻናት ሐኪሞችና ለማኅበራዊ አገልግሎት ሠራተኞች ግንዛቤ ማስጨበጥ ጠቃሚ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የሴቶች ግርዛት ጉዳይ በጤናና በማኅበራዊ ጉዳዮች ስርዓተ ትምሕርቶች ውስጥ እንዲካተቱ አሳስበዋል።ፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ግብጽና ቡርኪናፋሶን ጨምሮ በሌሎች የአፍሪቃ ሀገራት የሴቶች ግርዛትን የመከላከል ዘመቻ ከሚያካሂዱ ድርጅቶች አንዱ ነው።

Via DW
@Addis_Mereja
15.6K viewsedited  06:36
Buka / Bagaimana
2024-02-01 09:36:56
በፀጥታ ችግር ምክንያት ሶስት ፋብሪካዎቹን ስራ ማስጀመር አለመቻሉን ሞሐ የለስላሳ መጠጦች አስታወቀ!

በሀገሪቱ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ወደ ስራ መግባት እንዳልቻለ የገለፀው አዲሱ የሞሐ ለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አመራር በተቀሩት ፋብሪካው በተወሰነ ደረጃ ምርት ጀምሬያለሁ በማለት ገልጿል።ድርጅቱ በአጠቃላይ በአዲስ አበባ የሚገኙት ሶስቱ ፋብሪካዎች ጨምሮ ሐዋሳ ፣ መቐለ ፣ ጎንደር ፣ ደሴ እና ብሬ ቅርንጫፍ ፋብሪካ አለዉ።

"አሁን ባለዉ የፀጥታ ችግር ምክንያት በ 3 ፋብሪካዎችን አላስነሳንም" የሚሉት በሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አካለወልድ አድማሱ " ጥሬ እቃ መጓጓዝና ምርቱን ማከፋፈል ያስፈልጋል" ነገር ግን በተወሰኑት ፋብሪካዎቹ ያን ማድረግ አልተቻለም በዚህም ምርት አልተጀመረም ብለዋል።

ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ፔፕሲ፣ ሚሪንዳ አፕል፣ ሚሪንዳ ኦሬንጅ፣ ሚሪንዳ ቶኒክ እና በ7 ኣፕ ምርት ሲታወቅ ከ4 ወር በኃላ በድጋሚ በጀመረዉ ስራ እየተቆራረጠ ሲሰጥ የነበረዉ ምርቶቹን በቅርቡ ደግሞ በተሟላ ሁኔታ እንደሚጀምር ገልጿል።

ሞሐ ከደረሰበት ኪሳራ ለመዉጣት በባለቤቱ ውሳኔ ተደርገዋል በተባሉ መዋቅራዊ ለውጦች 45ኛ ድርጅት በመሆን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍን መቀላቀሉን ካፒታል ሰምቷል።

[Capital]
@Addis_Mereja
13.5K viewsedited  06:36
Buka / Bagaimana
2024-01-31 13:57:18 በአዳማ ወረዳ ተሰርቆ የተፈታታ ተሽከርካሪን ጨምሮ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ ተሰርቆ የተፍታታ ተሽከርካሪ ጨምሮ የተለያዩ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የአዳማ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

የአዳማ ወረዳ  ፖሊስ ወንጀል መርማሪ ክፍል ኃላፊ ሳጅን በሻ ዱቤ ለብስራት ቴሌቪዥንና ሬዲዮ  እንደገለፁት በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ መፈተሻ ኬላ ላይ በቁጥጥር ስር የዋለዉ ኮንትሮባንድ  ከ5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የተለያዩ እቃዎች ጨምሮ ተሰርቆ የተፈታታ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መነሻቸዉ ከጅቡቲ እና ከጅግጅጋ ከተማ እንደሆኑ የገለፁት ኃላፊዉ የተሰረቀ የተሽከርካሪ  እቃዎች ጨምሮ ኮስሞቲክ የተለያዩ አልባሳት እና የአይን መነፀሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን ገልፀዋል።


እነዚህን የኮንትሮባንድ እቃዎችን ሲያጓጉዙ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዉለዉ  የምርመራ መዝገባቸዉ ተጣርቶ  ለአቃቢ ህግ መላኩን ዋና ሳጅን ጨምረዉ ለጣቢያችን ገልፀዋል።

@Addis_Mereja
13.9K viewsedited  10:57
Buka / Bagaimana
2024-01-30 14:48:28 በነዳጅ የሚሰሩ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉ ተገለፀ

በነዳጅ የሚሰሩ አውቶሞቢሎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉን ያልሰሙ ሰዎች ገዝተው እያመጡ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ በዛሬው እለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ6 ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ገልፀዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ ምን አሉ?

ሚኒስትሩ "ማንኛውም የቤት አውቶሞቢል የኤሌክትሪክ ካልሆነ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ መንግስት ውሳኔ አስተላልፏል" ያሉ ሲሆን "ኢትዮጵያ ነዳጅ አታመርትም በጣም ውስን በሆነ የውጪ ምንዛሬ ሃብቷ ነው ከውጭ የምታስገባው" በማለት የመጀመሪያውን ምክንያት ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በስፋት መመረቱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ "ኤሌክትሪክ ኢትዮጵያ ላይ በብዛት ይመረታል እንደገና ደግሞ ከነዳጅ ጋር ሲነፃፀር የኤሌክትሪክ ዋጋ ርካሽ ነው" በማለት ሌላኛውን ምክንያት ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ "ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት አቀንቃኝ ነች ለዛም በትኩረት የምትሰራ ሀገር ነች" ያሉ ሲሆን የአየር ብክለትን ለመቀነስ ከነዳጅ ከሚሰራው አውቶሞቢል ይልቅ በኤሌክትሪክ የሚሰራው የሚመረጥ መሆኑን ተናግረዋል።

በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በአለም ላይ በስፋት እየተመረቱ መሆኑንንም ሚኒስትሩ የገለፁ ሲሆን በሀገራችን በከተማ አካባቢም ስለሚንቀሳቀሱ ቻርጅ ማድረጊያ መሰረተ ልማትን ማዳረስ የሚቻል መሆኑን ገልፀዋል።

በዚህም ማንኛውም ከውጭ የሚገባ የግል መገልገያ አውቶሞቢል የኤሌክትሪክ ብቻ መሆኑንን በማስመር ሚኒስትሩ "ይህን አልሰማንም" በሚል በነዳጅ የሚሰሩ አውቶሞቢሎችን ገዝተው ያመጡ መኖራቸውን ጠቁመው መከልከሉን ገልፀዋል።

@Addis_Mereja
12.6K viewsedited  11:48
Buka / Bagaimana
2024-01-23 09:16:06
ታሪክ አዋቂው እውቁ ጋዜጠኛ ገነነ መኩርያ (ሊብሮ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በኢትዮጵያ እግርኳስ ያለፉትን ሃምሳ አመታት በላይ በስፖርት ጋዜጠኝነት በታታሪነት ፣ በታሪክ አዋቂነት እና ሊብሮ ጋዜጣን በማዘጋጀት የሚታወቀዉ አንጋፋው ጋዜጠኛ ገነነ መኩርያ (ሊብሮ) በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።

@Addis_Mereja
19.7K viewsedited  06:16
Buka / Bagaimana
2024-01-23 09:16:06
በጋዜጠኞች እስር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሃገራት ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ሲፒጄ ገለጸ!

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ ሃገራት ሶስተኛ ደረጃ መያዟን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች (ሲፒጄ) ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል። በአፍሪካ በታሳሪ ጋዜጠኞች ብዛት ቀዳሚውን ቦታውን የያዘችው የኢትዮጵያ ጎረቤት ኤርትራ ስትሆን፤ ግብጽ ሁለተኛ ቦታን ይዛለች።

ሲፒጄ ዓመታዊ ሪፖርቱን ባጠናቀረበት ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ገደማ፤ በመላው ዓለም የታሰሩ ጋዜጠኞች ብዛት 320 እንደነበር ገልጿል። ይህ ቁጥር ድርጅቱ መሰል ሪፖርቶች ማዘጋጀት ከጀመረበት ከ1985 ዓ.ም. ወዲህ በከፍተኛነቱ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ መሆኑንም ጠቁሟል። የ360 ጋዜጠኞች እስር የተመዘገበበት የፈረንጆቹ 2022 ዓመት፤ የምንጊዜውንም ከፍተኛ ቁጥር ያስተናገደ ነው።

በአፍሪካ እስካለፈው ህዳር መጨረሻ ድረስ ባለው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ፤ ቢያንስ 67 የሚሆኑ ጋዜጠኞች “ከስራቸው ጋር በተያይዘ ለእስር መዳረጋቸውን” ሲፒጄ በሪፖርቱ አመልክቷል። ከእነዚህ ጋዜጠኞች ውስጥ አስራ ስድስቱን በማሰር እንዳለፉት ዓመታት ሁሉ በመጀመሪያ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኤርትራ ናት።

[Ethiopia Insider]
@Addis_Mereja
17.4K viewsedited  06:16
Buka / Bagaimana
2024-01-23 09:16:06
የታህሳስ ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት 28.7 በመቶ ሆኖ ተመዘገበ!

የታህሳስ ወር የዋጋ ግሽበት በህዳር ወር ከነበረበት 28.3 በመቶ ወደ 28.7 በመቶ በመሆን የተመዘገበ ሲሆን በዓላቱን ተከትሎ መጠነኛ ጭማሪ መኖሩን ከኢትዮጵያ ስታቲክስ አገልግሎት የተገኘው መረጃ ያመላክታል ።

በወሩ ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ምግብ ነክ ዕቃዎች (food items) 30.6 በመቶ ድርሻ የያዙ ሲሆን ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) 26.1 በመቶ በመሆን ሊመዘገብ ችሏል።

@Addis_Mereja
14.7K viewsedited  06:16
Buka / Bagaimana
2024-01-23 09:16:06
የአንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈፀመ

የአንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ የቀብር ስነ-ስርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ተፈፀመ፡፡ ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ባደረበት ህመም በአሜሪካ ሕክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ባለፈው ሳምንት ሕይወቱ ማለፉ ይታወቃል፡፡

@Addis_Mereja
14.1K viewsedited  06:16
Buka / Bagaimana
2024-01-18 19:30:36
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በመቀሌ በአሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ የመንሸራተት አደጋ እንዳጋጠመዉ አየርመንገዱ አስታወቀ!

በዛሬው ዕለት ከቀኑ በ06፡30 አካባቢ ከአዲስ አበባ ወደ በመቀሌ በረራ ያደረገው ET106 የመንገደኞች አውሮፕላን፤  በ08፡00 ሰዓት በአሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ካረፈ በኋላ የመንሸራተት እክል እንደገጠመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል፡፡

በጉዞው ላይ የነበሩ ሁሉም ሠራተኞች እና ተሳፋሪዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም መውረዳቸውን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል። የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን የገለጸው አየር መንገዱ፤ ለተፈጠረው እክል ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል።

@Addis_Mereja
15.2K viewsedited  16:30
Buka / Bagaimana