Get Mystery Box with random crypto!

Addis መረጃ™

Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™ A
Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™
Alamat saluran: @addis_mereja
Kategori: Berita
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 56.80K
Deskripsi dari saluran

@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹
.
⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬
⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬

መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


Pesan-pesan terbaru 8

2023-12-21 16:07:36
የሰሜን ኮሪያው መሪ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ለመጠቀም ዛቱ

የሰሜን ኮሪያው መሪ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ለመጠቀም ዳግም መዛታቸው ተነግሯል፡፡

የሀገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ባሰራጩት ዘገባ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን አሜሪካ ፤ደብቡ ኮሪያ እና ጃፓን የሀገሪቱ ባላንጣዎች በኑክለር ጦር መሳሪያ ቀጥተኛ ጥቃት እንደሚያደርሱባቸው የሚያጠራጥር አይደለም ብለዋል፡፡

ኪም በቅርቡ ሀገራቸው በሞከረችው የአህጉር አቋራጭ የባላስቲክ ሚሳይል ሙከራ የተሳተፉትን የሀገሪቱን ጦር ሀይል አባላት ባመሰገኑበት ወቅት ነው ይሄን ያሉት፡፡ ሰሜን ኮሪያ ባላንጣዎቿን ከኒክሌር ጦር መሳሪያዋ አደብ እንዲገዙ በግልጽ እንናገራለን ነው ያሉት፡፡

@Addis_Mereja
13.0K viewsedited  13:07
Buka / Bagaimana
2023-12-21 13:55:08 በአባተ አበበ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ተስፋዬ ወርዶፋ ፍርድ ቤት ቀረበ!

በአባተ አበበ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ተስፋዬ ወርዶፋ ኦዳ ፍርድ ቤት ቀረበ።የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የፖሊስን የጥርጣሬ መነሻና የተጠርጣሪውን መከራከሪያ ነጥብ ተመልክቷል።ተጠርጣሪው በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክ/ከተ ወረዳ 8 ነዋሪ መሆኑን አስመዝግቧል።

የአ/አ ፖሊስ መርማሪ ተጠርጣሪው በታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በከተማዋ በተለምዶ ቦሌ ኤድናሞል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከምሽቱ 4:00 ላይ አባተ አበበ የተባለ ግለሰብን በ3 ጥይት በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል ተብሎ መጠርጠሩን ጠቁሞ ምርመራ መጀመሩን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አብራርቷል።

በጅምር ምርመራ መዝገቡ የሰው ማስረጃ ቃል ለመቀበል እና የአስከሬን ምርመራ ውጤት ለማቅረብ የ14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት መርማሪ ፖሊስ ጠይቋል።የተጠርጣሪ ጠበቃ በበኩላቸው ደንበኛቸው ላይ ፖሊስ የጠየቀው የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ረጅም መሆኑን በመጥቀስ የተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ጥያቄውን በመቃወም ተከራክረዋል።

ጠበቃዋ ደንበኛዬ ስሜ በማህበራዊ ሚዲያ እየጠፋነው በማለት ፖሊስ ጣቢያ ለማመልከት እራሳቸው በሄዱበት ወቅት ነው የተያዙት በማለት ገልጸዋል።ደንበኛዬ በመገናኛ ብዙሃን እንደጥፋተኛ ተደርገው ንፁህ ሆኖ የመገመት መብታቸውን በጣሰ መልኩ እየተዘገበባቸው ነው በማለትም ጠበቃዋ አቤቱታ አቅርበዋል።

ጊዜ ቀጠሮ መዝገቡን የተመለከቱት ዳኛ በኩልም ተጠርጣሪ ተብሎ ቢዘገብ ችግር እንደሌለው ተገልጿል።እንደ አጠቃላይ የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ የጠየቀውን የምርመራ ማጣሪያ የ14 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።የምርመራ ማጣሪያ ውጤቱን ለመጠባበቅ ለታህሳስ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ተቀጥሯል።

Via FBC
@Addis_Mereja
12.6K viewsedited  10:55
Buka / Bagaimana
2023-12-17 08:48:02
የጥቁር አንበሳ የአየር ትርዒት እየተካሄደ ነው!!

የኢትዮጵያ አየር ኃይልና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ አየር ኃይል በጋራ "ጥቁር አንበሳ" የተሰኘ ልዩ የአየር ትርዒት እያካሄዱ ነው።

በመርሐ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ አየር ኃል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ኢብራሒም ናስር፣ ጄነራል መኮንኖች፣ የአፍሪካ አየር ኃይል አዛዦች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓል "በመስዋዕትነት ሀገርን የዋጀ፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል" በሚል መሪ ኃሳብ ከሕዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከበረ ይገኛል። በዛሬው ዕለትም የኢትዮጵያ አየር ኃይል የምሥረታ በዓል ማጠቃለያ መርኃ ግብር በአየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ እየተካሄደ ነው። በአሁኑ ሰዓት “የጥቁር አንበሳ የአየር ትርዒት” እየተካሄደ ይገኛል። የአየር ላይ ትርኢቱ የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች አየር ኃይል አባላት ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ጋር በመሆን ነው እያካሄዱት የሚገኙት።

@Addis_Mereja
18.3K viewsedited  05:48
Buka / Bagaimana
2023-12-13 10:41:40
የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አዲሱን 5 ቢሊየን ዶላር ሚያወጣ ‘የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከተማ’ ግንባታ በአራት ዓመታት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሠራ መሆኑን ገለጸ፡፡

አየር መንገዱ “ኤርፖርት ሲቲ” ብሎ የሚጠራውን ግንባታ ለመጀመር ከጫፍ የደረሰው እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለማርካት መሆኑን የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ የንግድ ሥራ ዘርፍ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ለማ ያደቻ ተናግረዋል፡፡

የ ‘ዓየር መንገድ ከተማው’ ካልተገነባ ዓየር መንገዱ በዘርፉ እያስመዘገበ ካለው ፈጣን ዕድገት አንጻር እንደሚፈተን ከግምት ውስጥ በማስገባት ፕሮጀክቱ መታቀዱን አብራርተዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 5 ቢሊየን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፥ በዓመት 100 ሚሊየን መንገደኞችን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል።

አሁን ላይ ዓየር መንገዱ በኦሮሚያ ክልል ከቢሾፍቱ ከተማ ጥቂት ወጣ ብሎ በሚገኝ ሥፍራ የመጀመሪያውን የ ‘ዓየር መንገድ ከተማ’ ግንባታ ለማስጀመር በዝግጅት ላይ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ዘመናዊ ሆቴሎች ፣አፓርትመንቶች፣ ከቀረጥ ነፃ የግብይት ሥፍራና የካርጎ ሎጂስቲክስ ማዕከል እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡ የአዋጭነት ጥናቱን በማጠናቀቅም ለዓለም አቀፍ ጨረታ ለማውጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል፡፡

(EPA)
@Addis_Mereja
15.4K views07:41
Buka / Bagaimana
2023-12-12 18:58:36 ታዬ ደንደአ ከመታሰሩ በፊት በድብቅ በአዳማ የተቀረጸ ድምፅ ቅጂ

ምንጭ :- ዘሀበሻ

@Addis_Mereja
14.2K viewsedited  15:58
Buka / Bagaimana
2023-12-12 17:14:09 የአማራ ክልል መንግስት የሰላም ጥሪ አስተላለፈ!

የአማራ ክልል መንግስት ከኃይል አማራጭን በመተው ወደ ሰላም ለሚመለሱ ኃይሎች የሰላም ጥሪ አስተላልፏል።

የክልሉ መንግስት ያወጣውን የሰላም ጥሪ አስመልክቶ የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር መንገሻ ፈንታው መግለጫ ሰጥተዋል።

የሰላም ጥሪው ተጨማሪ ደም መፋሰስን ለማስቀረት መንግስት በሆደ ሰፊነት የከፈተው የሰላም በር ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በጽንፈኝነት የተቃኘ እና የግል ፍላጎትን ማዕከል ያደረገ አላማ ባነገቡ ጥቂት ግለሰቦች እና ቡድኖች ቅስቀሳ የተሳሳቱ ወጣቶች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከስህተት መንገድ የሚመለሱበትን ሰላማዊ መንገድ ማመቻችት ስለሚገባ፤ በክልሉ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ ከህዝብ ጋር በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች የህግ የበላይነትን ባረጋገጠ አግባብ ለታጣቁ አካላት የሰላም ጥሪ ቀርቦ ግጭቱ እንዲያበቃ እና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ከህዝብ የተነሳውን ጥያቄ በመቀበል፤ ተጨማሪ ደም መፋሰስን፣ጥፋትን እና ውድመትን ለማስቀረት መንግስት በሆደ-ሰፊነት የሰላም አማራጮችን አሟጦ የመጠቀም ጥረቱን ማስቀጠል ለሃገር እና ለህዝብ ያለውን ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመርያ ዕዝ ጋር በመመካከር ስምምነት በተደረሰበት አቅጣጫ እና የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የወጣውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ  አዋጅ  ቁጥር 6 /2015 አንቀጽ 5(4) (ሠ) እና 6(12) መሰረት በማድረግ ይህ የሰላም ጥሪ የውሳኔ ሃሳብ ተላልፏል ሲል በመግለጫው አስታውቋል።

የውሳኔ ነጥቦቹንም እንደሚከተለው ጠቅሷል፣

1) ይህ ጥሪ ለህዝብ ይፋ ከተደረገ ጀመሮ በሚቆጠር ሰባት ቀናት ውስጥ በየትኛውም ኢመደበኛ አደረጃጀት እና ትጥቅ ትግል ውስጥ በመንቀሳቀስ ላይ ያሉ ታጣቂዎች ባሉበት አካባቢ በሚገኙ የኮማንድ ፖስት አዛዦች ለዚሁ አላማ ለይተው ለህዝብ ወደሚያሳውቋቸው የመሰብሰቢያ ስፍራዎች በመሄድ ወደ ሰላማዊ ህይወት ለመመለስ ያላቸውን ፍላጎት እንዲያሳውቁ ጥሪ ቀርቧል።

2) በየአካባቢው ያሉ የቀጠና ኮማንድ ፖስት አመራሮች፣ የአካባቢው አስተዳደር እና የፖለቲካ አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል ተወካዮች እና የሃገር ሽማግሌዎች ጋር በመተባበር ወደ ሰላማዊ ህይወት ለመመለስ ፍላጎት ኖሮዋቸው ወደ መሰብሰብያ ስፍራዎች ከላይ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚመጡትን ሁሉ በአግባቡ በመቀበል፣ የህክምና አገልግሎት እና መሰል አጣዳፊ አገልግሎት ለሚያስፈልጋቸውም አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ እንዲያስተናግዱ እና ወደተሃድሶ ማዕከላት እንዲወሰዱ መመሪያ ተሰጥቷል።

3) የቀጠና ኮማንድ ፖስት አመራሮች እና ተሃድሶ ማዕከላት አስተባሪዎች ወደ ሰላማዊ ኑሮ የሚመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች በተሃድሶ ማዕከላት ውስጥ አስፈላጊውን የተሃድሶ ስልጠና እንዲያገኙ፣ ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቅለው በሰላም ለመኖር የሚያስችላቸውን የአዕምሮ ዝግጅት ለማድረግ አስፈላጊው የሰነ-ልቦና፣ ምክር እና ሌሎች አስፈላጊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ በማድረግ የተሃድሶ መርሃ ግብር መጨረሳቸውን እያረጋገጡ የምስክር ወረቀት እንዲሰጡ መመሪያ ወርዷል።

4) ለህግ እና ፍትህ አካላት የተሃድሶ መርሃግብር ማጠናቀቂያ የምስክር ወረቀት ያገኙ የቀድሞ ታጣቂዎች በግጭቱ አውድ ውስጥ የተፈፀሙ በምህረት ሊሸፈኑ የሚችሉ ወንጀሎችን በተመለከተ የምህረት ተጠቃሚ እንደሆኑ በመገንዘብ እነዚህ ግለሰቦች ላይ ከነዚህ ወንጀሎች ጋር በተያያዘ የተጀመሩ የምርመራ፣ የክስም ሆነ የፍርድ ማስፈፀም ሂደቶችን በማቋረጥ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉ መመሪያ ተላልፏል።

5) የክልል፣ ዞን፣ ወረዳ እና ቀበሌ የፖለቲካ፣ የአስተዳደር አካላት እና አመራሮች ይህን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለሚመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ኑሮ መመለስ እንዲችሉ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉ፣ በተለይም እነዚህ ዜጎች በሰላማዊ እና ህጋዊ አግባብ የፖለቲካ ግብ እና አጀንዳቸውን ማራመድ ይችሉ ዘንድ ምቹ አውድ እና የውይይት መደረኮችን እንዲያመቻቹ መመሪያ ተሰጥቷል።

6) ይህንን የሰላም ጥሪ በየደረጃው ካሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እዞች ወይም ኮማንድ ፖስቶች ጋር በመቀናጀት እንዲያስፈፅም እና ለአፈፃፀሙ አስፈላጊ የሆኑ ዝርዝር መመሪያዎችን እንዲያወጣ ለክልልሉ የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊነት እና ስልጣን ተሰጥቷል።

7) የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ እዙ ጋር በመተባበር ይህ የሰላም ጥሪ ተግባራዊ ሆኖ በክልሉ ግጭት እና ሁከት እንዲቀር፣ህዝብም እፎይታ እንዲያገኝ ያለውን ቁርጠኝነት እየገለፀ ለዚህ ጥሪ ውጤታማነት አስተዋፅዖ ሊያበረክቱ የሚችሉ ባለድርሻ አካላት ሁሉ፣በተለይም የሃገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ለሰላም አጀንዳው መሳካት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪውን ያቀርባል።

በዚሁ አጋጣሚ ይህን ጥሪ ቸል በማለት የአመፅ እና የጉልበት መንገድ በሚመርጡ ግለሰቦች እና ታጣቂዎች ላይ የተጀመረው የህግ ማስክበር እርምጃ ተጥናክሮ እንደሚቀጥል ለማሳወቅ እንወዳለን ሲል ገልጿል።

@Addis_Mereja
14.1K viewsedited  14:14
Buka / Bagaimana
2023-12-11 19:12:22
ጠ/ሚ አብይ አህመድ አቶ ታዬ ደንዴአን ከስልጣን ማንሳታቸው ተሰማ!!

አቶ ታዬ ደንዴአ ከሰላም ሚኒስቴር ዴኤታነት መነሳታቸውን የጠ/ ሚኒስቴር ፅ/ ቤት ዛሬ በደብዳቤ አሳውቋቸዋል።

ደብዳቤው " ከመስከረም 28 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነዉ ላበረከቱት አስተዋጽኦ እያመስገንኩ ከታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከኃላፊነት የተነሱ መሆኑን አስታዉቃለሁ። " ይላል።

አቶ ታዬ ይሄን ፅሁፍ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፃቸው ቀጣዩ መልእክት አስፍረዋል።

"ለክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ

የተናገሩትንና የፃፉትን የመደመር እሳቤ አምኜ ተከተልኩዎት:: አሁን ግን በተናገሩት የማይኖሩ ብቻ ሳይሆን በሰዉ ደም የሚጫወቱ አረመኔ መሆንዎን ተረድቻለሁ:: እዉነት መስሎኝ በሀገር ህልውና ስም ሲያካሄዱ የነበረዉንና ኢትዮጵያውያንን ከማገዳደል አልፎ ሀገሪቷን ያደቀቃትን ከንቱ ጦርነት ሳዳምቅልዎ በነበረበት ወቅት ሲያወድሱኝ ነበር:: ዛሬ ነገሩ ገብቶኝ የወንድማማቾች መገዳደል ይቆም ዘንድ ለሰላም በመወገኔ ከስልጣን አነሱኝ:: ለወንበርና ለመኪና በመገዛት ኦሮሞን በኦሮሞ ለማጥፋትና ኦሮሞን ከወንድሞቹ ጋር ለማጣላት የሚጫወቱትን ቁማር እያየሁ ዝም ባለማለቴ እጅግ ደስተኛ ነኝ:: ስለነበረን አጭር ቆይታ አመሰግናለሁ:: እስካለሁ ድረስ ለሰላምና ለህዝቦች ወንድማማችነት የማደርገዉ ትግል ይቀጥላል! " ሲሉ በፌስቡክ ገፃቸው አስቀምጠዋል።

@Addis_Mereja
14.1K views16:12
Buka / Bagaimana
2023-12-10 11:08:16
ዜና እረፍት  

የቡናን ተክል በኢትዮጵያና በአለም ምርቱ እንዲስፋፋና እንዲታወቅ ከፍተኛ አስተዋጻኦ ያደረጉት፣ አቶ ይልማ የማነብርሃን በአጋጠማቸዉ የጤና እክል በአሜሪካን ሃገር በህክምና ሲረዱ ቆይተዉ በ89 እድሜያቸዉ ህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።    

አቶ ይልማ ዋ/ሥራ አስኪያጅ ሆነዉ በተለያዩ የመንግስትና የግል ድርጅቶች በከፍተኛ ብቃት እና ሃላፊነት በርካታ ብሮጀክቶችን ኣላማ በተሳካ ሁኔታ እየመሩ ለረጂም አመታት ያገለገሉ ሲሆን በእነዚህ ግዜያትም ሃገሪቱ በቡና ዘርፍ ተጠቃሚ እንድትሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፣ ቡናችንም በአለም እንዲታወቅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሰሩ፣ በዘርፉም ብዙ አንጋፋ ባለሙያዎችን ያፈሩ ነበሩ፡፡ 

ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ በሜድሮክ ኢትዮጵያ ስር በተቋቋመዉ  ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃ.የተ.የግል ማህበርን በመመስረት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የሰሩና በቡና እና ሻይ ታሪክ ትልቅ ድርሻ የነበራቸዉ በዚህም ምክንያት <የቡና አባት> የሚል ስያም የተስጣቸዉ አንጋፋ የሃገር ባለዉለታ ነበሩ።

አቶ ይልማ የማነብርሃን ያላቸዉን ትርፍ ግዜ ተጠቅመው ያካበቱትን እዉቀታቸውና ልምዳቸውን በመጽሃፍ መልኩ በማዘጋጀት “የኢትዮጵያ ቡና ልማት “ የሚል ቡና ከመሬት ዝግጅት ጀምሮ እስከ መጨረሻው ያለውን ሂደት የሚያሳይ በፎቶ ግራፍ የተደገፈ ጽሁፍ በአማርኛና በእንግሊዝኛ  ለትውልዱ አቅርበዋል፡፡

የአቶ ይልማ አስክናሬቸዉ በቅርቡ ወደ ሃገር ቤት መጥቶ ዘመድ አዝማድ ጎረቤት እና ጓደኞቻቸው በተገኙበት ስራአተ ቀብራቸዉ  እንደሚፈጽም በቤተሰቦቻቸዉ ተገልጸዋል፡፡
       
     ህዳር 29 ቀን 2016 ዓም

@Addis_Mereja
14.1K viewsedited  08:08
Buka / Bagaimana
2023-12-09 21:46:06
በኦሮሚያ ክልል የዜጎች ግድያና አፈና እንደቀጠለ ነው

በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ አደኣ በርጋ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት የኢንጪኒ ከተማ ባለሥልጣንና የጸጥታ አስከባሪዎችን ጨምሮ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

ስማቸው ለደህንነታቸው ሲባል እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ ፦ የሰባት ሰዎች አስከሬን ዛሬ ጠዋት ተገኝቷል። ማረሚያ ቤት ተሰብሮ እስረኞች ተለቀዋል፣ ህዳር 28 ቀን ለ29 ቀን 2016 ዓ.ም. አጥቢያ ከሌሊቱ ስድስት ሰኣት ጀምሮ ነው ጥቃት የተፈፀመው፣ የወረዳው ማረሚያ ቤት ተሰብሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞች ተለቀዋል ብለዋል።

በታጣቂዎቹ ጥቃት የከተማዋ አስተዳዳሪን (ብርሃኑ ሃብትዬ) ጨምሮ የሰዎች ህይወት አልፏል። በተለያዩ ጥበቃ ስራ የሚሰሩ እንዲሁም በማረሚያ ቤት ጥበቃ ላይ ነበሩ የተባሉ ፖሊሶችም መገደላቸውን ሰምተናል፣ ዛሬ ጠዋት ህዝቡ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ወጥቶ አስክረ ሲሰበሰብ ነበር። ቢያንስ ወደ ሰባት አስከሬን ተገኝተዋል፡፡ የተጎዱትም ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡

ሌላኛው ነዋሪ ፦ በወረዳው የፖሊስ ጣቢያ ላይም ጥቃት ደርሷል። የወረዳው መሳሪያ ግምጃ ቤትም ተሰብሯል መባሉን ጠዋት ሰምተናል፡፡ ሲንቄ ባንክ ላይም ከፍተኛ የመሰባበር ጉዳት ደርሷል፡፡ ሌሎች ባንኮች ግን ምንም አልሆኑም፡፡ ታጣቂዎቹ በያቅጣጫው ወደ ከተማው መግባታቸው ነው የተሰማው፡፡ እኛ ወጥተን ማየት ፈጽሞ የማይታሰብ ብሆንም ጠዋት እንደሰማነው ቁጥራቸው ከፍተኛ ነው ተብሏል፡፡

ሌላኛዋ ስማቸው እንዳይጠቀስ ያልፈለጉ ነዋሪ፣ አሁን ከቤት ለመውጣትም ሰግተናል፡፡ ወንድ ወንዱ ብቻ እየወጣ የሞቱትን ማንሳት ለቅሶ መድረስ ነው ያለው፡፡ ከተማዋ ጸጥ ብላለች፡፡ ሱቆችን ጨምሮ ምንም የተከፈተ ነገርም የለም።(ዶቼቬለ)

@Addis_Mereja
15.0K viewsedited  18:46
Buka / Bagaimana
2023-12-09 00:17:14 ለእሑድ ኅዳር 30 የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ መራዘሙ ተሰማ!

የፊታችን እሑድ ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ ሊካሄድ የታቀደው ሰላማዊ ሰልፍ ለሌላ ጊዜ መራዘሙን አስተባባሪ ኮሚቴው አስታውቋል።

ኮሚቴው ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰልፉ ለሌላ ጊዜ የተላለፈው መንግስት አራት የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴን ማሰሩን ጨምሮ «አሉታዊ» የተባሉ እርምጃዎች በመወሰዳቸው ነው ብሏል፡፡

ኮሚቴው በዛሬ ከሰዓቱ ጋዜጣዊ መግለጫው ከ2011 ዓ.ም. ጀመሮ በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ እና ሌሎችም አከባቢዎች በተደረጉ ጦርነቶች ሞት፣ አካል መጉደል እና የንብረት ውድመት መከሰቱን አስታውሷል፡፡ በጦርነት ሂደቱም አስገድዶ መደፈር ጨምሮ የተለያዩ በደሎች በተዋጊዎች በማህበረሰቡ ላይ መድረሱን በሰብዓዊ መብት ተቋማት ጭምር መረጋገጡንም እንዲሁ፡፡ግጭቶቹ “ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሃገርን ለዘርፈ ብዙ ምስቅልቅል ከመዳረግ አልፎ ለውል አልባ የማፍረስ አደጋ ሊዳርግ የሚችል” ያለው የሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴው ሰልፉ የተጠራው “ጦርነት ይቁም! ሰላም ይስፈን!” በሚል መሪ ቃል የፖለቲካ ልዩነቶች በሰላም እንዲፈቱ በማለም ነበር ብሏልም፡፡

ኮሚቴው ይህንኑን ሰልፍ ለማካሄድ የሚመለከተውን የመንግስት አካል ባሳውቅም መንግስት ሰልፉን የማክሸፍ ስራ ሰርቷል ነው ያለው፡፡ በጋራ የተዘጋጀውን መግለጫ ለጋዜጠኞች ያነበቡት ከአስተባባሪዎቹ አንዱ የሆኑት አቶ ዘለሌ ፀጋስላሴ ናቸው፡፡ በተነበበውም መግለጫ “መንግስት ሰላማዊ ሰልፉን የተለያዩ ፀረ-ሰላም ሃይሎች ያዘጋጁት እንደሆነ በማስመሰል የሰልፉ ቀን የጸጥታ ሃይሎችን የማሰማራት ፍላጎት የሌለው መሆኑን በመግለጽ ሰላማዊ ሰልፉን አቅጣጫ በማሳት አደናቅፏል” ተብሏል፡፡

በመሆኑም ኮሚቴው የሰልፉን ቀን ለሌላ ጊዜ ለማስተላለፍ መገደዱን አስረድተዋል፡፡ “የሰልፉ ዓላማ ግልጽ ነው፡፡ በአገራችን ጦርነት እንዲቆም በማድረግ የሚደርሰውን እልቂትና ውድመት ማስቀረት ነው፡፡ ሆኖም መንግስት የህዳር 30ውን አገር አዳኝ ሰልፍ ከመደገፍ ይልቅ ሰልፉን ከታለመለት ዓላማ ውጪ በመግፋቱ አስተባባሪ ኮሚቴው ለተወሰኑ ቀናት በመግፋት ሰልፉን በተሻለና በውጤታማ መንገድ ለማካሄድ መደምደሚያ ላይ ደርሷል” ነው የተባለው፡፡

የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል ትናንት ማምሻውን ባወጣውና ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ ግን “በሰላማዊ ሰልፍ ሽፋን አዲስ አበባን የሁከትና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ የሽብር ተልዕኮ ተቀብለው በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች ሴራ ከሸፈ” ሲል ማስታወቁ ይታወሳል።

@Addis_Mereja
13.6K viewsedited  21:17
Buka / Bagaimana