Get Mystery Box with random crypto!

Addis መረጃ™

Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™ A
Logo saluran telegram addis_mereja — Addis መረጃ™
Alamat saluran: @addis_mereja
Kategori: Berita
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 56.80K
Deskripsi dari saluran

@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹
.
⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬
⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬

መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


Pesan-pesan terbaru 3

2024-03-02 10:18:37
128ኛ የዐድዋ ድል በአዲስ አበባ እየተከበረ ሲሆን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩ ነህ በፖሊስ ማርች ታጅበው በአፄ ምኒሊክ ሀውልት ስር ጉንጉን አበባ አኑረዋል።

በዓድዋ ድል መታሰቢያም ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

@Addis_Mereja
13.4K viewsedited  07:18
Buka / Bagaimana
2024-03-01 17:57:15 የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሊያ የአየር ክልል በኩል መብረር አቆመ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስያ አገራት ለሚያደርጋቸው በረራዎች ይጠቀምበት በነበረው የሶማሊያ የአየር ክልል በኩል መብረር ማቆሙን አስታወቀ።አየር መንገዱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከሶማሊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች “አስተማማኝ የአየር ትራፊክ አገልግሎት” ባለማግኘቱ እንደሆነ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ለቢቢሲ አማርኛ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስያ ለሚደርጋቸው በረራዎች “ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ” ይጠቀምበት በነበረው የሶማሊያ አየር ክልል መብረር ያቆመው፤ የአየር መንገዱ አውሮፕላን ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የካቲት 16/2016 ዓ.ም. በአገሪቱ የአየር ክልል ውስጥ ካጋጠመው ክስተት ጋር በተያያዘ መሆኑን አቶ መስፍን አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን፤ “በዓለም አቀፍ አሠራር መሠረት እንደዚህ ዓይነት ነገር ሲያጋጥም ለሚመለከታቸው የሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣናት ሪፖርት እናደርጋለን። [የቅዳሜውን ክስተት በተመለከተም] ለሶማሊያ እና ለኢትዮጵያ የሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣናት ሪፖርት ተደርጓል” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ይሁንና እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩን አክለዋል።የቅዳሜ ዕለቱ ክስተት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሊያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚሰጠውን አገልግሎት “አስተማማኝ ሆኖ እንዳያገኘው” ማድረጉን አቶ መስፍን ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት ይህ ክስተት ካጋጠመበት ማግስት እሁድ የካቲት 17/2016 ዓ.ም. አንስቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሶማሊያን አየር ክልል መጠቀም ለማቆም መወሰኑን አስታውቀዋል።አቶ መስፍን፤ ከክስተቱ በኋላ ካለው ቀን አንስቶ “አማራጭ ለመጠቀም ወስነናል። ለዚህም ዋናው ምክንያት [የቅዳሜ ዕለቱ ክስተት] ነው። እዚያ በነበረው ሁኔታ፤ የአየር ክልሉ አስተማማኝ የአየር ትራፊክ አገልግሎት ስላላገኘንበት ለደኅንነት ስንል አማራጭ መንገዶች እየተጠቀምን ነው” ሲሉ የአየር መንገዱን ውሳኔ አብራርተዋል።

አየር መንገዱ ወደ እስያ ለሚያደርጋቸው በረራዎች የሚጠቀመው የሶማሊያን የአየር ክልል እንደነበር ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ በአሁኑ ሰዓት እነዚህ በራረዎች የሚደረጉት በጂቡቲ አየር ክልል በኩል መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጂቡቲን የአየር ክልል እየተጠቀመ ያለው “ተጨማሪ ወጪ በማያመጣ መልኩ” እንደሆነም አክለዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሌለሎች አገራት ለሚደረጉ በራረዎች የሶማሊያን አየር ክልል መጠቀም ቢያቆምም ወደ ሞቃዲሾ እና ወደ የሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሀርጌሳ ከተማዎች የሚያደርጋቸውን በራረዎች “ያለ ችግር” መቀጠሉን አብራርተዋል።

Via BBC
@Addis_Mereja
13.9K viewsedited  14:57
Buka / Bagaimana
2024-02-29 11:18:06 ጋና የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን በተመለከተ ጠንካራ ሕግ አጸደቀች!

የጋና ፓርላማ ከተመሳሳይ ፆታ ግንኙነቶች እና በዚህ ዙሪያ ከሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ በሚከሰሱ ሰዎች ላይ ጠንከር ባለ እስር የሚቀጣ ሕግ አጸደቀ።አዲሱ ሕግ በተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ውስጥ መሆናቸውን የሚገልጹ እንዲሁም ሆነው የተገኙ ሰዎችን እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ እስር፣ ቡድኖችን የሚያቋቁሙ እና በገንዘብ የሚደግፉ እስከ አምስት ዓመት እስር እንዲቀጡ ያደርጋል።

የአገሪቱ ሕግ አውጪዎች የእስር ቅጣቱ ወደ ማኅበረሰብ አገልግሎት እና የምክር ድጋፍ እንዲቀየር የተደረገውን ጥረት ተቃውመው ውድቅ አድርገውታል።በአገሪቱ ሁለት ዋነኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተደገፈው እና ፓርላማው ያጸደቀው ይህ ሕግ ተግባራዊ የሚሆነው የጋናው ፕሬዝዳንት ናና አኩፎ-አዶ በፊርማቸው ሲያጸድቁት ነው።ፕሬዝዳንቱ ቀደም ሲል አብዛኛው የአገሪቱ ዜጎች የሚፈልጉት ከሆነ ሕጉን እንደሚያጸድቁት ተናግረው ነበር።

የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት በጋና ውስጥ ቀደም ብሎም ሕገወጥ ሆኖ በሦስት ዓመት እስር የሚያስቀጣ ነው።ሕጉ “በሰዎች መሠረታዊ መብት እና ነጻነት ላይ ከባድ አደጋን የሚደቅን ነው” ሲል ባለፈው ወር አምነስቲ ኢንተርናሽናል ተቃውሞውን አሰምቶ ነበር።የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት መብት ተቆርቋሪዎች አሁን የወጣው ሕግ ሰዎችን እና በዚህ ዙሪያ የሚሠሩ ማኅበራትን ለማሳደድ ስለሚውል አንዳንዶች ለመደበቅ ይገደዳሉ ብለዋል።

Via BBC
@Addis_Mereja
13.5K viewsedited  08:18
Buka / Bagaimana
2024-02-26 16:41:12 ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ባለስልጣን ጋር አብሮ የነበረ ፈረንሳያዊ ጋዜጠኛ ኢትዮጵያ ውስጥ ታሰረ ተባለ

ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋለ። ጋዜጠኛው  በቁጥጥር ስር የዋለው ባለፈው ሐሙስ የካቲት 14 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ሲሆን፤ «ረብሻ ለመቀስቀስ » ሞክረሃል መባሉንም ቀጣሪው ድርጅት አስታውቋል። አንቷን ጋሊንዶ የተባለው ጋዜጠኛ በቅርቡ የተካሄደውን የአፍሪቃ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤን አፍሪቃ ኢንተለጀንስ ለተሰኘ ልዩ ኅትመት ለመዘገብ ነበር ወደ አዲስ አበባ የተጓዘው።

ጋዜጠኛው ባለፈው ቅዳሜ የካቲት 16 ቀን፣ 2016 ፍርድ ቤት መቅረቡን የገለጸው አፍሪካን ኢንተለጀንስ እስከ ፊታችን አርብ የካቲት 22 ቀን፣ 2016 ዓ/ም ድረስ እስሩ እንደተራዘመ ማረጋገጡን ዳጉ ጆርናል ከዶቼዌሌ ዘገባ ተመልክቷል። ጋዜጠኛው «ያለምክንያት መታሰሩን » እንደሚቃወምም  ገልጻል።

የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት አንድ  ማንነቱ እንዳይገለጥ የፈለገ ለጉዳዩ ቅርበት ያለው ምንጭ  ነገረኝ እንዳለው ከሆነ  ጋዜጠኛው አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ ሐሙስ ከሰአት የተያዘው ከአንድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ባለስልጣን ጋር በተገናኘበት ወቅት ነበር ተብሏል።

አንድ የኦነግ አንድ ቃል አቀባይ ሐሙስ ዕለት አዲስ አበባ ውስጥ የፓርቲያቸው አንድ አባል መታሰሩን ግን ከጋዜጠኛው ጋር በተገናኘ ይሁን አይሁን ማረጋገጥ እንደማይችሉም ለየፈረንሳይ ዜና አገልግሎት  ተናግረዋል። 

የአፍሪቃ ኢንተለጀንስ ኅትመት የምሥራቅ አፍሪቃ ክፍልን በኃላፊነት የሚመራው የ36 ዓመቱ ጋዜጠኛ እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር ከ2013 እስከ 2017 ኢትዮጵያ የኖረ እና «በኢትዮጵያ የመገናኛ አውታር ባለሥልጣናት»ም የሚታወቅ ነው ሲል የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት አክሎ ዘግቧል። የኢትዮጵያ መንግስት ባለሥልጣናት በጉዳዩ ላይ ምላሽ አለመስጠታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

Via ዶቼዌሌ

@Addis_Mereja
15.3K viewsedited  13:41
Buka / Bagaimana
2024-02-25 20:45:08
በተመሳሳይ ከፍታ ርቀት ላይ በመጓዝ ላይ የነበሩት የኳታር እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ስህተት ምክንያት ከመጋጨት ለጥቂት መትረፋቸዉ ተነግሯል።

ንብረትነቱ የኳታር አየር መንገድ የሆነዉ አዉሮፕላን ( ኳታር 6 ዩ) ከዶሃ ተነስቶ ወደ ኡጋንዳ ኢንቴቤ በ 38,000 ጫማ ከፍታ ላይ ሲበር የነበረ ቢሆንም በሞቃዲሾ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አዉሮፕላኑ ወደ 40,000 ጫማ ወደላይ እንዲወጣ ተነግሮታል።

በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 6 : 32 ገደማ በተመሳሳይ በ39,000 ጫማ ከፍታ ርቀት ላይ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ዱባይ ሲጓዝ ከነበረዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዉሮፕላን ( ኢቲ 602) ጋር የተፋጠጠዉ የኳታር አዉሮፕላን ከመጋጨት ለጥቂት መትረፉ ተዘግቧል።ሁለቱ ካፒቴኖች ስለ ክስተቱ ሲነጋገሩ የተቀረጹት ቅጂዎች ሁለቱም በሞቃዲሾ ከሚገኙ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የተሳሳተ መመሪያ እንደተቀበሉ ያሳያል ተብሏል።

በሁለቱም አውሮፕላኖች ላይ የተገጠመው የግጭት ማስወገጃ ሲስተም (TCAS) ወዲያውኑ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፣ ይህም በታዘዘው ከፍታ ላይ ሌላ አውሮፕላን መኖሩን በማመልከቱ ምክንያት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወት እንዲተርፍ ለማድረግ መቻሉ ዝግባዎች አመላክተዋል።ይህን ተከትሎ በሞቃዲሾ የሚገኙት የፀጥታ ኃይሎች በሶማሊያ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የሆኑትን ሙባረክ ኑር አሊን በቁጥጥር ስር እንዲዉል አደርገዋል።

Via Capital
@Addis_Mereja
14.0K viewsedited  17:45
Buka / Bagaimana
2024-02-24 16:32:30
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የዶ/ር ካሳ ተሻገርን ያለመከሰስ መብት አነሳ!

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 16፤ 2016 ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ፤ የየካ ምርጫ ክልል ተወካይ የሆኑትን የዶ/ር ካሳ ተሻገርን ያለመከሰስ መብት አነሳ። የዶ/ር ካሳ የህግ ከለላ የተነሳው፤ “በአማራ ክልል ተደራጅቶ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ይንቀሳቀሳል” ከተባለ “ጸረ ሰላም ኃይል” ጋር “ትስስር ያላቸው” እና “ለቡድኑ መመሪያ ይሰጡ የነበረ በመሆኑ ነው” ተብሏል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@Addis_Mereja
13.0K viewsedited  13:32
Buka / Bagaimana
2024-02-22 11:37:48
ገዳም ውስጥ የነበሩ "አራት አባቶች በኦነግ ሸኔ" ተገደሉ!

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ውስጥ እራሱን "ኦነግ ሸኔ" ብሎ የሚጠራው ቡድን የገዳሙን መጋቢ ጨምሮ አራት አባቶችን መግደሉን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክስርቲያን አስታወቀች።

የቤተ ክርስቲያኗ የህዝብ ግንጙነት መምሪያ ካወጣው መረጃ አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2016 ታጣቂዎቹ ሦስት አባቶችን አግተው ወደ በረሃ ከወሰዱ በኋላ የታገቱትን ለማስለቀቅ ገዳሙ ጥረት በሚያርግበት ወቅት የካቲት 13 ቀን 2016 ተጨማሪ አባቶችን እና የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች እንደተገደሉና አብረው ከነበሩት አንድ አባት ብቻ ማምለጥ መቻላቸውን ተገልጿል፡፡

እንዲሁም የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች ቡድኑ ከዚህ ቀደም ገዳሙን በመዝረፍ ለከፋ ችግር አጋልጦት መቆየቱን አስታውሰው ገዳሙ ጸጥታውን የሚያስከብረበት መሣሪያዎች በቡድኑ በመወረሳቸው ምክንያት ለከፋ የጸጥታ ችግር መጋለጡን አንስተዋል፡፡በአሁኑ ወቅት ገዳማውያኑ በስጋት ላይ መሆናቸውም የተገለጸ ሲሆን፤ የመንግሥት የጸጥታ አካላትን እገዛ እንደሚሹ አዲስ ማለዳ ከመምሪያው ያገኘችው መረጃ ያመላክታል።

[Addis Maleda]
@Addis_Mereja
17.9K viewsedited  08:37
Buka / Bagaimana
2024-02-21 09:37:27
አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሳ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ሌሊቱን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል::

አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሳ...

ሀገሬን አትንኳት
መሄዴ ነው
አዲስአበባ
ሳይሽ እሳሳለሁ
ክፈቺውና መስኮቱን
የከረመ ፍቅር
ትዝ ባለኝ ጊዜ ...በሚሉና ሌሎችም ተወዳጅ ዘፈኖች ይታወቅ ነበር::

ጌታቸው ካሳ በየካቲት 12 ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቷል ::

Via Sheger
@Addis_Mereja
17.5K viewsedited  06:37
Buka / Bagaimana
2024-02-20 11:16:50
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት መቋረጥ እንዳጋጠመው ገለፀ

በባንኩ መረጃ ማስተላለፊያ የፋይበር ኦፕቲክስ ገመድ ላይ በደረሰ ጉዳት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሟል።

አገልግሎቱን መልሶ ለማስጀመር ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት በከፍተኛ እርብርብ እየተሰራ ያለው ባንኩ ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።

@Addis_Mereja
16.3K viewsedited  08:16
Buka / Bagaimana
2024-02-15 18:52:36 የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት ፈተና (12ኛ ክፍል) የተፈታኞ ምዝገባ በሚመለከት ለሚዲያ አካላት ማብራሪያ ሰጥቷል።

የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ ምን አሉ ?

- የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ለፈተና ከመቀመጣቸው በፊት የመመዝገቢያ መስፈርቱን ማሟላት አለባቸው። በተቀመጠው የጊዜ ገድብ ውስጥም መምዝገብ አለባቸው።

- ምዝገባዉ የሚከናወነዉ በበይነመርብ /Online Registration / አማካኝነት ሲሆን ከየካቲት 3 -30/2016 ዓ.ም
ይሆናል።

- በየደርጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትኩርት ማድርግ ያለባቸውን ጉዳዮችም የሚከተሉት ናቸው ብለዋል ፦

1ኛ. ተፈታኞች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መምዘገብ አለባቸው። ከየካቲት 3 -30 /2016 ዓ.ም ብቻ።

2ኛ. ምንም አይነት ስህትት ማለትም የፆታ ߹የስም ስህተት߹የፎቶ ߹የትምህርት መስክ እና የመሳስሉት ችግሮች እንዳይፈጠሩ በትኩርት መስራት መቻል አለባቸው።

3ኛ. ከየካቲት 30 /2016 ዓ.ም በኃላ የሚመጣ ምዝገባ ተቀባይነት እንደሌለዉ ማወቅ አለባቸው።

4ኛ. የመደበኛና የማታ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወንው በተማሩበት ት/ቤት ይሆናል።

5ኛ. የግል ߹ የርቀት /የበይነ መርብ /ተፈታኞ ምዝገባ በክፍለ ከተማ ߹በወርዳና ትምህርት ፅ/ቤቶች ይሆናል።

Via Ethio FM
@Addis_Mereja
25.3K viewsedited  15:52
Buka / Bagaimana