የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የዶ/ር ካሳ ተሻገርን ያለመከሰስ መብት አነሳ! የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 16፤ 2016 ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ፤ የየካ ምርጫ ክልል ተወካይ የሆኑትን የዶ/ር ካሳ ተሻገርን ያለመከሰስ መብት አነሳ። የዶ/ር ካሳ የህግ ከለላ የተነሳው፤ “በአማራ ክልል ተደራጅቶ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ይንቀሳቀሳል” ከተባለ “ጸረ ሰላም ኃይል” ጋር “ትስስር ያላቸው” እና “ለቡድኑ መመሪያ ይሰጡ የነበረ በመሆኑ ነው” ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @Addis_Mereja 13.0K viewsedited 13:32