2024-01-22 13:00:52
ዜና መረሐቤቴ!
የፋሽስቱ ዘራፊና ቀማኛ ሰርጎ ገብ ቡድን በመርሐቤቴ ንፁሃን ላይ አሰቃቂ ግፍ ፣ግድያ እና ዝርፊያ እየፈጸመ ነው።
እስከዛሬ ድረስ አልደፈር ያላችሁን እናንተ ናችሁ በማለት ህዝቡን ለመበቀል እየሰራ ነው።
1/ ከለሚ በኩል የተንቀሳቀሰው ዘራፊ ቡድን ፌጥራ ላይ የህዝቡን ጤና ጣቢያ እና ባንኮችን ዘርፏል።
2/ ከወደ ዘመሮ የገባው ግሪሳ መንጋ ደግሞ ሁለት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጥበቃዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ትምህርት ቤቶችን ዘርፏል፣አውድሟል።
3/ እንድ ትልቅ አረጋዊ አባትን ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ እናንተ ለፋኖ እየጸለያችሁ ነው ጥይት የማይመታቸው በማለት በአሰቃቂ ግድያ ገድለው ገደል ጥለዋቸዋል።
4/ ከዘመሮና ከለሚ የመጣው ኃይል በአንድ ላይ ሆኖ የአርበኞች ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጥሶ በመግባት እያፈረሰ ምሽግ አሳድጎታል ።
5/ ሌሎች አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችንም እንደዚሁ ዘረፋ ላይ ነው። ።
ይህንን ተከትሎ ጀግናው የመርሐቤቴ ወጣት ጥምቀት ላይ አይፈራም መሬ፣ አይፈራም!
መች ተዋጋና
የገባን ማስወጣት ባህላችን አይደለም እያለ ሲወርፋቸው ውሏል።
ህዝባችንን የጨፈጨፈና መሰረተ ልማቶቻችንን ያወደመ የጠላት ሃይል እንዳይወጣ ህዝቡ እምቢተኝነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥልና በጋራ እንድንፋለም ሲል አንድ አማራ ፋኖ ጥሪውን አስተላልፏል።
13.3K viewsG T, 10:00