2024-01-21 20:48:54
ከመብረቁ ብርጌድ የተሰጠ አጭር ወቅታዊ ወግለጫ
ዉሸት ግብሩ የሆነዉ የብልፅግና ኦህዴድ አገዛዝ አገልጋይ የሆነዉ የምርኮኛዉ ብረሃኑ ጁላ ጦር በዛሬዉ እለት የአማራ ፋኖ መብረቁ ብርጌድን በተመለከተ ፍፁም ዉሸት የሆነ መግለጫ አዉጥተዋል፡፡ ይሁን እንጅ ከህዳር 23/2016 ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ የዉጊያ ግንባሮች ማለትም በሰላ ድንጋይ ፤በደብረ ብርሃን ከተማ እና አካባቢዉ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ድል ማስመዝገባችን በተለያዩ የሚዲያ አዉታሮች መግለፃችን ይታወሳል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢዉ የሚኖረዉ ሁሉም ማህበረሰባችን እና ቀደምሲል በብልፅግና ዉስጥ ሆነዉ አገዛዙን ሲያገለግሉ የነበሩ ጠቅላላ የሞጃ እና ወረዳ አመራሮች ጭምር ከፋኖ ጎን ሆነዉ በመታገላቸዉ ምክንያት ብስጭት ዉስጥ የገባዉ አገዛዙ በሚከተሉት ጉዳዮች ከላይ መግለጫ አዉጥተዋል፡፡
1ኛ መላዉ ህዝባችን የሚያዉቀዉ የመብረቁ ብርጌድ ዋና አዛዥ ሸለቃ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ሆኖ ሳለ ‹ፍቃዱ› የሚባል በአመራርም ሆ በአባል የሌለ ስም በመጥቀስ የብረጌዱን መሪ ገድለናል በሚል የወጣዉ መግለጫ የስርዓቱ የተለመደ ዓይን ያወጣ መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡
2ኛ ዉሸት ግብሩ የሆነዉ የአገዛዙ ቡድን ከዚ በፊት በአማራ ፋኖ ላይ ሲያደርግ የነበዉ ስም የማጥፋት ዘመቻ ማለትም (የተበተነ ነዉ፤ ዱቄት ሆኗል፤ የአቅመ ቢሶች ስብስብ ነዉ ወዘተ) በማለት ለሌሎች ወንድምና እህት ኢትዮጵያ ን በዉሸት መፈብረኪያ ማሽኖቹ የሚያሰራጨዉን የዉሸት ፕሮፖጋንዳ በመቀልበስ ፋኖ የደረሰበትን የእዉቀት እና የአቅም ደረጃ በግልፅ ለማሳየት በማይንቀሳቀሱ መኪኖች ላይ የብትር ሽፋን ወይም ብረት ለበስ ተሸከርካሪ በመስራት በቀጥታ የስርኣቱ አሽር የሆነዉ የምረኮኛዉ ብርሃኑ ጁላ ጦር እንዲያደገኘዉ እና በቅጥፈት ማስተጋቢያ ሚድያ እነዲያቀርበዉ በማሰብ በአገዛዙ ሰራዊት ቅርብ ርቀተ ላይ ተቀምጦ የነበር አገልግሎት የማይሰጥ ብረት ለበስ ተሽከርካሪ እሱ እነደማረከዉ አድርጎ ማቅረቡ የአገዛዙን የመጨረሻ የዉድቀት ደረጃ የሚያሳይ ነዉ፡፡
የብርጌዳችንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ፡- የምርኮኛዉ ብርሃኑ ጁላ ጦር እንደሚለዉ በሰላ ድንጋይ እና አካባቢዉ የተደመሰሰ እና የተበተነ ሳይሆን የሞጃ እና ወደራ ወረዳ መቀመጫ የሆነችዉን ሰላድንጋይ ከተማን ጨምሮ ሁሉንም የወረዳዉ ቀበሌዎች ፤የባሶ እና ወራና ወረዳ ሁሉንም ቀበሌወጭ እንዲሁም በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደተር ዉስጥ ከሚገኙ ቀበሌወች ከግማሽ በላይ የሆኑትን የምናስተዳደር መሆኑን እያሳወቅን የሰሜን ሸዋ ዞን መቀመጫ የሆነችዉን ደብረ ብርሃን በተመለከተ በፈለግኑ ቀን እና ሰዓት ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር አቅም እንዳለን ህዝባችን እንዲያዉቅልን እንፈልጋለን፡፡
ጥር 12/05/2016 ዓ/ም
ደብረ ብርሃን ሸዋ
#Follow
facebook 1 :- https://www.facebook.com/profile.php?id=61554383356900&mibextid=2JQ9oc
facbook 2:- https://www.facebook.com/asharamedia24
Youtbe :- https://www.youtube.com/channel/UCPmgFzP2ZPmdGjHxXjigJaw
telegram:- https://t.me/asharamedia24
Watsapp:- https://whatsapp.com/channel/0029Va5CGsH2ER6bIAUd2L1T
13.5K viewsደምሳሽ የማርያም!, edited 17:48