Get Mystery Box with random crypto!

Ashara Media - አሻራ ሚዲያ

Logo saluran telegram asharamedia24 — Ashara Media - አሻራ ሚዲያ A
Logo saluran telegram asharamedia24 — Ashara Media - አሻራ ሚዲያ
Alamat saluran: @asharamedia24
Kategori: Politik
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 5
Deskripsi dari saluran

ስልክ፥ 251984190114 / 251993111700

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 9

2023-11-17 12:23:21 ሰሜን ጎንደር ዳባት
ሰሞኑን በአጅሬ ጃኖራ የነበረው ውጊያ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ለሊት ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር ከነዋሪዎቹ ያገኘሁት መረጃ ያመላክታል። ሰሞኑን በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከባድ የሚባል ሰብዓዊ ጉዳት ደርሷል። በጎንደር ሆስፒታል እንዲሁም አይራ አካባቢ ያሉ ጤና ጣቢያዎች በርካታ ቁስለኞች መግባታቸውን ከህክምና ባለሙያዎች ያገኘሁት መረጃ ይጠቁማል።

አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:-
#Youtube:- Ashara Tv - https://www.youtube.com/channel/UC2LZu_N0iOJipVUw3RyR4Ng#facbook:- https:www.facebook.com/asharamed4
#ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedi#instagram:- https://instagram.com/asharamediaofficial?utm_source=qr&igshid=MzNlNGNkZWQ4Mg==
#ዋትስአፕ :-https://whatsapp.com/channel/0029Va5CGsH2ER6bIAUd2L1T#
12.9K viewsG T, edited  09:23
Buka / Bagaimana
2023-11-17 10:26:44
የቅዱስ ላሊበላ ገዳም አለም አቀፍ ቅርስ አስተዳዳሪ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው ካህናት ተገድለዋል፣ ተደብድበዋል፣ ታስረዋል ተባረዋል ብለዋል።

በሰላማዊ ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል ብለዋል። ሙሉ መግለጫውን ከላይ ያንብቡ።

አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:-
#Youtube:- Ashara Tv - https://www.youtube.com/channel/UC2LZu_N0iOJipVUw3RyR4Ng#facbook:- https:www.facebook.com/asharamed4
#ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedi#instagram:- https://instagram.com/asharamediaofficial?utm_source=qr&igshid=MzNlNGNkZWQ4Mg==
#ዋትስአፕ :-https://whatsapp.com/channel/0029Va5CGsH2ER6bIAUd2L1T#
13.1K viewsG T, edited  07:26
Buka / Bagaimana
2023-11-16 18:30:01
የአፍሪካ ልማት ባንክ ሁለት ሰራተኞች በጸጥታ ሀይሎች ድብደባ እና ህገወጥ እስር እንደተፈጸመባቸዉ ተቋሙ አስታወቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ በኢትዮጵያ ሁለት ሰራተኞች በጸጥታ አካላት ድብደባ እና ህገወጥ እስር ተፈጽሞባቸው እንደነበር አስታዉቋል።

ተቋሙ በዛሬው እለት ካወጣዉ መግለጫ ዳጉ ጆርናል እንደተመለከተው ፤ ጉዳዩ ጠ/ሚ ዐቢይ ጋር የደረሰ መሆኑ የተሰማ ሲሆን ጣልቃ ገብተዉ ሰራተኞቹ በአፋጣኝ እንዲፈቱ ማድረጋቸዉን ተቋሙ ገልጿል። ተቋሙ ጠ/ሚኒስትሩ ላደረጉት ነገርም ምስጋናዉን ሰጥቷል።

ይህ በጣም አሳሳቢ የሆነ ዲፕሎማሲያዊ ክስተት ነዉ ያለዉ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፤ ኢትዮጵያ ባለስልጣናት ይፋዊ ቅሬታ ማቅረቡንም ጠቅሷል።

ተቋሙ በኢትዮጵያ የሚገኙ ሰራተኞቹ ወደ አገራቸው የሚጓዙት በቪየና የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ኮንቬንሽን እንዲሁም በአፍሪካ ያለውን መብት ፣ ጥቅምና ዲፕሎማሲያዊ ያለመከሰስ ሙሉ በሙሉ እንደሚከበሩ መንግስት ለአፍሪካ ልማት ባንክ አረጋግጧልም ነዉ ያለዉ።

ከሰሞኑ የአፍሪካ ልማት ባንክ የአዲስአበባ ቢሮዉን ዘግቶ ወጥቷል የሚሉ የተሳሳቱ መረጃዎች ሲሰራጨቱ መቆየታቸውንም ዳጉ ታዝቧል።

መነሻውም የኢትዮጵያ መንግስት የተበደረገውን 5 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ የአፍሪካ ልማት ባንክ ነን በሚል በተላከ ኢሜል ከተጨበረበረ በኋላ መሆኑም ይታወሳል።
13.4K viewsG T, 15:30
Buka / Bagaimana
2023-11-16 10:50:44 << 66 በመቶ ኢትዮጵያውያን የጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን ዘመን ገደብ እንዲኖረው ይፈልጋሉ >> - የአፍሮ ባሮ ሜትር ጥናት
<< በኢትዮጵያ የስልጣን ሁኔታ በተለይ የጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን እንዲገደብ የሚፈልገው ኢትዮጵያዊ ቁርጥ ከ66 በመቶ በላይ ማለፉን >>አፍሮ ባሮ ሜትር አስታወቀ።

ተቋሙ ይሄን ያለው ባለፉት ሶስት ተከታታይ አመታት ያስጠናውን ጥናት ተከትሎ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ሲሆን በ2015 ዓ.ም ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት በኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የስልጣን ዘመን እንዲገደብ የሚፈልገው ቁጥር እያሻቀበ መጥቷል ብሏል።

በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ህገ መንግስት እንዲቀየር የሚፈለገው ቁጥርም ከፍ እያለ መምጣቱን ተቋሙ ይፋ አድርጓል።

< የፌዴራል መንግስቱ የስራ ቋንቋ እንዲጨመር እና ሌሎች ቋንቋዎች እንዲካተቱበት የሚፈልጉት ቁጥርም ክፍተኛ ነው > ብሏል።

ባለፉት ሶሶት አመታት ያካሄደውን ዳሰሳ ጥናት አስመልክቶ መግለጫ የሰጠው አፍሮባሮሜር አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባን ደረጃ ወደ ክልል ከፍ እንዲል ወይም የፌዴሬሽኑ አባል ክልል እንዲሆን እንደሚሹም አክሎ ጠቁሟል።

በተጨማሪም ህገ መንግስቱን ሙሉ ለሙሉ ከመተካት ወይም አሁን ባለበት እንዲቀጥል ከማድረግ ይልቅ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ፍላጎት ለማንፀባረቅ እንዲያስችል መሻሻል አለበት የሚሉት ኢትዮጵያውያን በርካቶች መሆናቸውን አመላክቷል።

አፍሮ ባሮ ሜትር ያወጣው የዳሰሳ ጥናት  የፖለቲካ ልሂቃኑን በሚያወዛግቡ ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች ላይ የህዝቡ አስተያየት ምን እንደሚመስል ያካተተ ሲሆን በአንድ በኩል ህዝባዊ ድጋፍ ያለው በሌላ በኩል ደግሞ ጉልህ ተቃውሞ እንዳለው ለማረጋገጥ ችያለሁ ባይ ነው።

ልዩነቶች ከተስተዋሉባቸው ጉዳዮች መካከልም የኢትዮጵያ ህዝቦች ብሄሮችና ብሄረሰቦች የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት የሚሰጠውን አንቀፅ 39ኝን ከህገ መንግስቱ ይወገድ ወይስ ይቀመጥ የሚለው ይገኝበታል። 

በተጨማሪም በብሔራዊ ሰንደቅ አላማው ላይ ያለው አርማ ይነሳ ወይም ይቀጥል የሚለው እንደሚገኝበት ነው የተመላከተው።

በተመሳሳይ አዲስ አበባን የፌዴሬሽን ምክር ቤት  አባል እንድትሆን የሚፈልጉት ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከ35 በመቶ ወደ 53 በመቶ ከፍ ማለቱን ተቋሙ ያወጣው የዳሰሳ ጥናት አረጋግጦ ይፋ አድርጎታል።

በሌላ በኩል ፌዴራላዊ የአስተዳደራዊ ስርዓቱን በሚመለከት አስጠንቼ ደርሸበታለሁ ያለውን ውጤት ይፋ ያደረገው አፍሮባሮሜትር ፌዴራላዊ ስርዓቱን በሚመለከትም ኢትዮጵያዊ ከሁለት መከፈሉን ይፋ አድርጓል።

ግማሽ ያህሉ ኢትዮጵያዊ ማለትም 49 በመቶ የሚሆነው ፌዴራላዊ አወቃቀሩ መሆን የሚገባው ብብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ማንነት መሰረት ባደረገ አግባብ ነው ሲል ሌላኛው 48 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ክልልሎች በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጣቸውና ገፅታቸው እንጂ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች በሚኖሩበት መልኩ መሆን የለበትም ባይ መሆናቸውን አመልክቷል።

በተመሳሳይ ከተሜው ኢትዮጵያዊ መልክዓ ምድራዊ ገፅታዎችን ማዕከል ያደረገ የፌዴራል ስርዓት የመምረጥ ዝንባሌ ያሳዩት ቁጥር 54 በመቶ የሚሆኑት ሲሆኑ በገጠር የሚገኙ ነዋሪዎች ማለትም  51 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ በበኩላቸው ማንነትን መሠረት ያደረገ የፌዴራል ስርዓትን መርጠዋል ብሏል።
አሻም

አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:-
#Youtube:- Ashara Tv - https://www.youtube.com/channel/UC2LZu_N0iOJipVUw3RyR4Ng#facbook:- https:www.facebook.com/asharamed4
#ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedi#instagram:- https://instagram.com/asharamediaofficial?utm_source=qr&igshid=MzNlNGNkZWQ4Mg==
#ዋትስአፕ :-https://whatsapp.com/channel/0029Va5CGsH2ER6bIAUd2L1T#
13.6K viewsG T, edited  07:50
Buka / Bagaimana
2023-11-14 16:55:13 የፕሬዝዳንቷ ጥገኝነት መጠየቅ | የጋዜጠኞች መታፈን | ያልተመለሱ ጥያቄዎች - ከምክርቤቱ

12.9K viewsናፍቆት !, 13:55
Buka / Bagaimana
2023-08-27 19:04:54 https://www.youtube.com/live/muxTCe2abVU?si=RjtCC13Qd8PK3p9w
13.1K views16:04
Buka / Bagaimana
2023-08-24 17:50:10
13.6K views14:50
Buka / Bagaimana
2023-08-24 17:49:39
13.0K views14:49
Buka / Bagaimana