Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Digital Library

Alamat saluran: @ethiopian_digital_library
Kategori: Pekerjaan
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 64.54K
Deskripsi dari saluran

በዚህ ቻናል
👉ትምህርታዊ መፅሐፎችን
👉ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎችን
👉የሶሻልና የናቹራል መጽሐፎችን
👉የዩኒቨርስቲ እና የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
👉የጥያቄና መልስ ወርክ ሽቶችን እና
👉ልዩ ልዩ መጽሐፎችን በነፃ ያገኛሉ!
For any comments: @ethiodlbot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 6

2024-04-28 13:33:30
ልዩ የመምህራንና የትምህርት አመራር የአቅም ማጎልበቻ የክረምት ስልጠና

ትምህርት ሚኒስቴር በቀን14/08/2016 ዓ.ም በቁጥር፡- 10/242/897/2016 በተፃፈ ደብዳቤ በትምህርት ስርዓቱ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መኆኑን በመግለጥ ከዚህም መካከል የመምህራንንና ትምህርት አመራሮችን አቅም ለመገንባት በክረምት ልዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መርሃ ግብርን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለመጀመሪያ ዙር የሚሰጥ ይሆናል::

በመሆኑ በዚህም ዙር በእንግሊዝኛ፣ ሂሳብ፣ በፊዚክስ፣ በኬሚስትሪ እና ባዮሎጂ የትምህርት መስኮች በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነትና በትምህርት አመራርነት በመስራ ላይ ያሉት ስልጠና የሚሰጥ ይሆናል፡፡ #የአዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር_ትምህርት_ቢሮ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.4K viewsedited  10:33
Buka / Bagaimana
2024-04-26 14:06:43 የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር ይሰጣል

12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል።

የዩንቨርሲቲ መውጫ ፈተና ሰኔ መጀመሪያ ከተሰጠ በኋላ የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ይሰጣል።

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ እንዳደረጉ መገለፁም ይታወሳል፡፡

ለሦስተኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ለማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.3K viewsedited  11:06
Buka / Bagaimana
2024-04-25 17:04:15
የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የኦሮሚያ ትምህርት ትራንስፎርሜሽን ታክስ ፎርስ ተቋቁሞ እየተሰራ ነው - ኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ

በክልሉ በርካታ ጎበዝ ተማሪዎችን ለማፍራት የተለያዩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው እየተሰራ እንደሚገኝ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ ገልፀዋል፡፡

ቢሮው የኦሮሚያ ልማት ማህበር ካስገነባው ልዩ አዳሪ ትምህርት ፣ በክልሉ መንግስት ከተገነቡ ቦረና ሆስቴል እና ዶዶላ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ልምድ በመቅሰም ተማሪዎችን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ በመመልመል በልዩ ትምህርት ቤቶች አንዲማሩ እያደረገ እንደሚገኝም ነው ኃላፊው ያነሰቱ፡፡

ከዚህ በፊት የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ከ600 በላይ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር ውስን እንደነበር የገለፁት ዶ/ር ቶላ በክልሉ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥርን ለማሳደግ ልዩ አዳሪ እና ልዩ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የመማር ማስተማር ስርዓቱ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡

በዚህም አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጸው ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት እና ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ የሚችሉ ተማሪዎችን በብዛት ለማፋራት ትኩረት ተሰጥቶችት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.5K viewsedited  14:04
Buka / Bagaimana
2024-04-25 15:48:44
በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥር የሚገኙት ዘንዘልማ እና ሰባታሚት ካምፓሶች በፀጥታ ችግር ምክንያት መዘጋታቸውን ሪፖርተር ዩኒቨርሲቲውን በመጥቀስ ዘግቧል

በሁለቱ ካምፓሶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የግብርና፣ የጤና፣ የጂኦሎጂ እና የዲዛስተር ማኔጅመንት ተማሪዎች የፀጥታው ችግር እስኪቀረፍ ከተማ ውስጥ ባሉ ካምፓሶች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ማድረጉን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ብርሃኑ ገድፍ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በዘንዘልማ እና በሰባታሚት ካምፓሶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ በርካታ ተማሪዎች ከተማ ውስጥ ያሉ ካምፓሶች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው፡፡

ዘንዘልማ እና ሰባታሚት ካምፓሶች በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ በየጊዜው እንደሚሰማ የገለፁት ም/ፕሬዝዳንቱ፤ በተማሪዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ከአንድ ወር በፊት ወደተለያዩ የተቋሙ ካምፓሶች እንዲዘዋወሩ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

በከተማዋ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች ውስጥ በቂ ቦታ በመኖሩ ተማሪዎቹ ምንም ዓይነት መጉላላት ሳይደርስባቸው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው ብለዋል፡፡

አሁን ላይ ከሁለቱ ካምፓሶች ውጪ በሌሎች ካምፓሶች ላይ ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር እንደሌለ ም/ፕሬዝዳንቱ ገልጸው፤ በባህር ዳር ከተማ ካለው አንፃራዊ ሰላም አኳያ በርካታ ተማሪዎች ምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

ከሁለቱ ካምፓሶች ውጪ አለመረጋጋቱ የተሻሻለ ቢሆንም፤ አልፎ አልፎ የተኩስ ድምፅ እንደሚሰሙ ተማሪዎቹ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮ ተመራቂዎች የምረቃ ቀን መቼ እንደሆነ እስካሁን እንዳልተነገራቸውም አክለዋል፡፡ #ሪፖርተር

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.7K views12:48
Buka / Bagaimana
2024-04-23 10:36:16 የሪሚዲያል ፈተና

የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ፈተና ከሰኔ 3 -14 በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል!

#Remedial

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.8K viewsedited  07:36
Buka / Bagaimana
2024-04-23 10:18:29
ሚያዝያ 15 (April 23) ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ቀን

የዓለም መጽሐፍ ቀን በየዓመቱ ሚያዝያ 15 ይከበራል።

ሚያዝያ 15 ለዓለምአቀፍ የመጽሐፍ ቀንነት የተመረጠበት ምክንያት የዊልያም ሼክስፒር እና ስፔናዊው የታሪክ ጸሐፊ ኢንካ ጋርሲላሶ ዴ ላ ቬጋ የሞቱበት ቀን በመሆኑ እንደመታሰቢያ እንዲሆን ነው።

በእዚህ ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ በተለይ ወላጆች ለልጆቻቸው መጻሕፍትን በስጦታ መልክ በመስጠት ያከብሩታል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.0K viewsedited  07:18
Buka / Bagaimana
2024-04-22 16:05:43
በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የተሰሩ ሞዴሎች የቁንጅና ዉድድር ሊካሄድ ነዉ

እስካሁን በተለመዱት የቁንጅና ዉድድሮች ሴቶች ባላቸዉ ቁንጅና ተወዳድረዉ የቁንጅና አክሊል ይሸለሙ ነበር፡፡ አሁን ግን ውድድሩ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ውጤት በሆኑ ሞዴሎች መካከል ነው ይለናል የዴይሊ ሜይል ዘገባ፡፡

"ሚስ ኤ.አይ" የተሰኘዉ የቁንጅና ውድድር በዓለም አቀፉ የኤ.አይ ፈጣሪዎች ሽልማት አዘጋጆች (The World AI Creator Awards) ተሰናድቷል፡፡ ዓላማውም በዓለም አቀፍ ደረጃ የኤ.አይ ፈጠራ ስራ ዉስጥ ለሚሳተፉ አካላት እውቅና ለመስጠት ብሎም ለማበረታታት ነው። ሰዉ መሳይ ሮቦት ሞዴሎችን በመስራት ላይ ያሉ አካላት ምርቶቻችዉን በማስመዝገብ በውድድሩ ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡

ተወዳዳሪ ሞዴሎቹ የተለያዩ የውበት እና መሰል መለኪያዎችን ያካተተ አጠቃላይ ግምገማን እንዲያልፉ ይደረጋል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያላቸዉ ተፅዕኖ ፈጣሪነትና እዉቅናም ከግምት ውስጥ የሚገባ ይሆናል።

ውድድሩ ኤሚሊ ፔሌግሪኒ እና አይታና ሎፔዝ በተባሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰሩ ሁለት ታዋቂ ሞዴሎችን ጨምሮ በአራት ባለሙያዎች ይዳኛል። የዉድድሩ አሸናፊዎች የሚጋሩት 20 ሺ ዶላር የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን ከቁንጅና መለኪያ ዘዉድ ጋር አሸናፊዋ ትቀዳጃለች፡፡

ምንጭ:- የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.4K viewsedited  13:05
Buka / Bagaimana
2024-04-22 15:56:04 በ2016 ዓ.ም 8.8 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል - ትምህርት ሚኒስቴር

በፀጥታ ችግር ምክንያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 8.8 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በኢትዮጵያ በግጭት ምክንያት 8,977 ትምህርት ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 6,483 ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆናቸውን በሚኒስቴሩ 'ትምህርትን በአደጋ ማስቀጠል' ባለሙያ ንጋቱ አበበ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስቴሩ እና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በጋራ በመሆን የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል ጥረት ቢያደርጉም፤ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች በቀጠሉት ግጭቶች ምክንያት ችግሩን ለመፍታት አስቸጋሪ እንደሆነ ባለሙያው ጠቁመዋል፡፡

የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ባለሙያው ጥሪ አቅርበዋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.1K viewsedited  12:56
Buka / Bagaimana
2024-04-21 12:48:06
500 ብር የመክፈል እና ደረሰኝ የማቅረብ ግዴታ

የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የአገልግሎት 500 ብር የመክፈል እና ደረሰኝ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው - ትምህርት ሚኒስቴር


ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ #ExitExam #Exit_Exam

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.9K viewsedited  09:48
Buka / Bagaimana
2024-04-21 11:33:38 #Inbox

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ከመጣ ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲ መምህራን በተለያዩ ስብሰባዎች የተናገራቸው ወይም ቃል የገባቸው ግን ፈፅሞ ያልተገበራቸው፦

1. ለዩኒቨርሲቲ መምህራን ክብራቸውና ደረጃቸውን የሚመጥን በቂ የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግ ጠንክረን እንሰራለን።

2. ለሶስተኛ ድግሪ (ፒኤችዲ) ተማሪዎች በቂ የምርምር ገንዘብና ጥቅማ ጥቅም ጭማሪ ይደረጋል አይደለም ጭማሪ ሊያደርግ ጭራሽ GAT ፈተና ለመፈተን 1000 ብር መመዝገቢያ ብሎ የሚከፈለኝ ወርሃዊ ደመወዝ ወር እስከ ወር አላደረሰኝም ከሚል መምህር ገንዘብ መሰብሰብ ጀመረ።

3. ከክልልና ከዞን ከተማ መስተዳድር አካላት ጋር ተነጋግረን ለዩኒቨርሲቲ መምህራን ቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጥ እናደርጋለን።

4. ብዙ ዓመት በማስተርስ ያስተማረ መምህርና አዲስ ማስተርስ የያዘ መምህር በፍፁም ተመሳሳይ ደመወዝ መከፈል የለባቸውም፤Horizontal እና Vertical career structure ተግባራዊ እንዲሆን እናደርጋለን።

5. ከአሁን በኋላ የዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሹመት በብሄርና በ recommendation ሳይሆን በእውቀት (merit-based) እንዲሆን እናደርጋለን።

6. ከአሁን በኋላ ለመማር ማስተማር የሚያገለግሉ ግብአቶች  በበቂ ሁኔታ በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሟሉ ይደረጋል።

የማይተገብሩትን ቃል መግባት እዳ ብቻ ሳይሆን ታማኝነትንና አመኔታን ያሳጣል።

To: የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር

CC: ለፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

From: ሙሳ ሙሃባ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
13.1K viewsedited  08:33
Buka / Bagaimana