ብቻ ምን መሰለህ ትንሽ ስራ ስትጀምር የሚተችህ መብዛቱ አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር እንደነገረኝ ከሆነ ከ7 አመት በፊት ተጨማሪ ተጓዳኝ ስራ ልጀምር ብዬ ዲሽ መግጠም ጀመርኩ አለ። ታዲያ በሰዓቱ የገጠመኝ ነገር ይገርማል አለኝ። ምን መሰለህ የስራ ባህላችን እጅግ መቀየር አለበት! የስራ ባልደረቦቼ ሳይቀሩ አንተ እኮ ይህን ስራ መስራት የለብህም ምን ሆነህ ነው ይሉኝ ነበር። ለአንተ ይሄ አይመጥንህም ተው አታሰድበን እስከ ማለት ደርሰውም ነበር። አንድ ቀን ደግሞ እንዲሁ ተደውሎልኝ ስሄድ የተማሪዎቼ ቤት ኖሯል ከዚያማ ከላይ ወጥቼ እየሰራሁ ቲቹ ነው እኮ እየሰራ ያለው ደሞዙ አንሶት ነው አሁን ይህን የሚሰራ ሲሉ ሰማዋቸው። ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰፈር የሚያውቀኝ ሰው አንተ መምህርም አይደለህ ለምንድን ነው ከአቧራ ጋር የምትታገለው አሁን የመምህር ደሞዝ አልበቃህ ብሎህ ነው ሲል የዲሽ ጥገናውን እንዳቆም አሳስቦኝ ነበር። ብቻ ምን መሰለህ ትንሽ ስራ ስትጀምር የሚተችህ መብዛቱ አለኝ! እና አሁን የኤሌክትሮኒክስ ጥገና ከፍቼ ጥሩ የሚባል ስራ እየሰራሁ እገኛለሁ በመምህርነቱም እየሰራሁ ነው ። ያው እንደምታውቀው ቅርብ ጊዜ ኑሮው እጅግ በመናሩ ብዙ መምህራን ጓደኞቼ ሲቸገሩ አያለሁ እኔ ግን ብዙ ጫና ቻል አድርጌ በመስራቴ ኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም ችያለሁ ። ሳጠቃልልህ የስራ ባህላችን በጣም መስተካከል አለበት የሚሰራን ሰው ለማደናቀፍ የሚደረጉ ብዙ ጥረቶች አሉ ቢቻል ብናበረታታው ካልተቻለ ደግሞ ዝም ብን ሲል GA ሃሳቡን አጠቃሏል ። እናንተስ ምን ትላላችሁ? @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library 13.1K viewsedited 12:21