በአማራ ክልል 3000 በላይ ትምህርት ቤቶች በዘንድሮ የትምህርት ዘመን ተዘግተዋል! በአማራ ክልል በተከሰተው የጸጥታ ቀውስ ምክንያት 2.6 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሲሆኑ፤ ከ3000 በላይ ትምህርት ቤቶችም በዘንድሮ የትምህርት ዘመን ተዘግተዋል። በፌደራል መንግስት እና በፋኖ ሀይሎች መካከል እየተካሄደ ያለው ውጊያ ለዚህ አሳሳቢ ችግር ዋነኛ መንስኤ ነው። በድርቅ በተጎዱ የአማራ ክልል አካባቢዎች በዚህ የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን ከክልሉ የትምህርት ቢሮ ባለስልጣናት የተገኙ ሪፖርቶች አመልክተዋል። #አዲስ_ስታንዳርድ @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library 13.0K viewsedited 14:55