በኦሮሚያ ክልል መሬት ያልወሰዱ መምህራን ለመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው ታዘዘ በኦሮሚያ ክልል የመኖሪያ ቤት የሚሰሩበት መሬት ላልወሰዱ የክልሉ መምህራን ቦታ እንዲሰጣቸው የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ትእዛዝ መስጠታቸውን የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። የክልሉ የትምህርት ቢሮ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በአዳማ ከተማ ውይይት አድርጎ 8 የውሳኔ ሀሳቦችን ያስተላለፈ ሲሆን ከ8ቱ ነጥቦች አንዱ በከተማ ቤት መስሪያ ቦታ ላልወሰዱ መምህራን በአስቸኳይ ሊሰጣቸው ይገባል የሚል እንደሆነ ተጠቅሷል። ከዚህ ቀደም መምህራኑ የቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው መመሪያ ወጥቶ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ከቆይታ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች እገዳ ተጥሎ እንደነበርና በክልሉ ት/ት ቢሮ ጥያቄ መሰረት ዳግም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ለመምህራኑ እንዲሰጣቸው ትእዛዝ መሰጠቱ ተጠቁሟል። ጉዳዩም ተፈፃሚ እንዲሆን የኦሮሚያ መሬት ቢሮ ለተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ትዕዛዝ መስጠቱም ተገልጿል። @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library 13.0K viewsedited 13:17