Get Mystery Box with random crypto!

የመምህራን ደመወዝ በመከፈሉ በወላይታ ዞን የተቋረጠው ትምህርት ተጀምሯል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል | Ethiopian Digital Library

የመምህራን ደመወዝ በመከፈሉ በወላይታ ዞን የተቋረጠው ትምህርት ተጀምሯል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን፣ ላለፉት ሁለት ወራት ያህል ታጉሎ የቆየው የመምህራን ደመወዝ በመከፈሉ የተቋረጠው የመማር ማስተማር ሒደት መቀጠሉን፣ የክልሉ የመምህራን ማኅበር አስታወቀ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ዐማኑኤል ጳውሎስ፣ ችግሩ ተፈጥሮባቸው የነበሩት የአንድ ከተማ አስተዳደር እና የ20 ወረዳዎች ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ መመለሳቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፡፡

ለደኅንነታቸው ስለሚሰጉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ውስጥ የሚያስተምሩ የአካባቢ ሳይንስ መምህር፣ ለሁለት ወር ያህል የታጎለባቸው ደመወዝ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም. በመከፈሉ ከሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም. አንሥቶ ተቋርጦ የቆየው ትምህርት መቀጠሉን በስልክ ተናግረዋል፡፡

መምህራን ወደ ሥራቸው የተመለሱት፣ የሁለት ወር ደመወዛቸው በከፊል እና ሙሉ በሙሉ በመከፈሉ መኾኑን፣ ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁት ሌላው መምህር ገልጸዋል፡፡ #VOA

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library