Get Mystery Box with random crypto!

ድምፀ ተዋሕዶ (VoT)

Logo saluran telegram onesinod — ድምፀ ተዋሕዶ (VoT)
Logo saluran telegram onesinod — ድምፀ ተዋሕዶ (VoT)
Alamat saluran: @onesinod
Kategori: Agama
Bahasa: Bahasa Indonesia
Pelanggan: 26.86K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


Pesan-pesan terbaru 2

2023-05-22 17:21:19
ስብሰባው ተጠናቋል!

ሲኖዶሱ ጉባኤውን አጠናቋል። ውሳኔም አሳልፏል። ሐምሌ 9 ሹመት ይከናወናል። ከኦሮሚያ 7 ሰው ከደቡብ 2 ሰው እንዲሾም ተወስኗል። የሚሾሙት ከሕገ ወጡ ነው አይደለም የሚለው አልተገለጸም።
ዝርዝሩን ድምፀ ተዋሕዶ ይዛ ትቀርባለች።

ድምፀ ተዋሕዶ
https://t.me/onesinod
21.9K viewsedited  14:21
Buka / Bagaimana
2023-05-22 13:36:14
መምህር ብርሃኑ አሁን ተፈተዋል።
ትኩረት ወደ ሲኖዶሳችን!
21.2K views10:36
Buka / Bagaimana
2023-05-22 13:21:50 ትኩረት ወደ ሲኖዶሳችን

መምህር ኃይለማርያምም የአበውን በረከት ቀመሱ። መምህር ብርሃኑም እንዲሁ በረከት አገኙ። የታሠረ ይፈታል፤ የማይመለሰው የሞተ ብቻ ነው።
ጆሮዎች ሁሉ ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ ያዘንብሉ!
19.4K views10:21
Buka / Bagaimana
2023-05-22 11:50:40
ሌላ የግፍ ዜና

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መምህሩ እና የሀገሬ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅ መምህር ብርሃኑ አድማስ ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ከቢሯቸው በጸጥታ ኃይሎች ተወስደዋል።

ድምፀ ተዋሕዶ
https://t.me/onesinod
48.0K viewsedited  08:50
Buka / Bagaimana
2023-05-21 22:14:09
ለታሪክ ይቀመጥ። ራሱ ያወጣውን ሕግ የማይፈጽም ብሮድካስት ባለሥልጣን። አንረሳውም!
18.6K views19:14
Buka / Bagaimana
2023-05-21 22:07:38 ጠቅላይ ቤተ ክህነትን ፌዴራል ተቆጣጥሮታልን?

በማኅበራዊ ሚዲያ ቤተ ክህነት በፌዴራል ኃይል ቁጥጥር ሥር ዋለ የሚል መረጃ እየተዘዋወረ ነው። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ቤተ ክህነቱን ፌዴራል ተቆጣጥሮታል የተባለው ሐሰት ነው። እስካሁን ሲጠብቁ ከነበሩ የፌዴራል ፖሊሶች ውጭ የተለየ ነገር የለም።
ይህ ማለት ከደቂቃ በኋላ አዲስ ነገር ላይፈጠር ይችላል ማለት አይደለም። መረጃዎችን በየሰአቱ እናደርሳችኋለን።

ድምፀ ተዋሕዶ
https://t.me/onesinod
16.9K views19:07
Buka / Bagaimana
2023-05-21 21:13:19
በዚህ ቻናል ውስጥ ብፁዓን አባቶቻችን እንዳላችሁ እናውቃለን። የነገው ቀን ካወቃችሁበት በታሪክ ስማችሁ ጎልቶ የሚጻፍበት፣ ካላወቃችሁበት ግን በነፍስም በሥጋም የምትጠየቁበት ነው።
አባቶቻችን በደማቸው አጽንተው ያቆይዋትን ቤተ ክርስቲያን እናንተ ለብሔርተኛ አሳልፋችሁ ከሰጣችሁት ስለ ሃይማኖቱ ዋጋ የሚከፍለው ንቁ ኦርቶዶክሳዊ ከእናንተ ትከሻ ላይ አይወርድም። የትኛውም አይነት ጫና ቢደርስባችሁ ጫናው ሊያሸንፋችሁ አይገባም። ሞት እንኳን ቢመጣ ብትሞቱ ለክብራችሁ ነው። እናንተ የሞታችሁት እኮ የመነኮሳችሁ ዕለት ነው።
በስብሰባችሁ ውስጥ
1, ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚታገሉትን
2, ለፖለቲካ የቆሙትን
3, በዝምታ ውስጥ ሆነው በሁለት ቢላ የሚበሉትን ለይተን አውቀናቸዋል። ስም የማንጠቅሰው የጉባኤያችሁ ፍጻሜ እስከሚደርስ መታገሱ ተገቢ ስለሆነ ነው።
በመጨረሻም፣ ስለ እውነት ቆማችሁ የመነኮሳችሁላትን እና ዓለምን የተዋችሁላትን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቃላችሁ ወይስ ለፖለቲካ በመሸጥ ታሪካችሁን አበላሽታችሁ የምትመሩትን ምእመን ታሳዝናላችሁ!
ብፁዓን አበው መልሱን ለእናንተ ትተናል። ጥቁር ልበሱ ስትሉን ጥቁር ለብሰን ያነባነው ከፊት ስለተሰለፋችሁልን እና ለቤተ ክርስቲያናችን ሟች መሆናችንን ስናረጋግጥላችሁ ነው።
ቤተ ክርስቲያን ከእናንተም ከማንም በላይ ናት። አደራችንን ተቀብላችሁ ስማችሁን በወርቅ ቀለም እንደምትጽፉ ተስፋ እናደርጋለን።

ድምፀ ተዋሕዶ
https://t.me/onesinod
16.7K views18:13
Buka / Bagaimana